×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:20

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ - ክፍል አንድ Featured

Rate this item
(0 votes)

የመጽሐፍ ግምገማ

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ - ክፍል አንድ

 

አቶ መርኪና በሰማንያ ሦስት ዓመታቸው በኅዳር ወር 2000 ዓ.ም. ወደ ጌታ ተሻግረዋል። በቀብራቸው ሥርዓት ላይ ከስምንት ሺህ በላይ ሰው እንደ ተገኘ ታውቋል። ይህ ክፍል “የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክና የወላይታ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ታሪክ” በሚል ግለሰቡ ጽፈው በ 2000 ዓ.ም. ከታተመው መጽሐፍ የተቀነጨበ ነው። ከዚህ ቀደም እንዳደረግነው ሁሉ መጽሐፉን ከመገምገም ይልቅ ከተለያዩ የመጽሐፉ ክፍሎች ቆንጽሎ በማስነበብ አንባቢዎቻችንን በጌታ ሥራ ማደፋፈር የተሻለ እንደ ሆነ ተገንዝበናል። ከ 13 ዓመት በፊት አቶ አማኑኤል አብርሃም “የሕይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ ካሳተሙት መጽሐፍ ጋር ተመሳሳይነት አለው። የሚያስገርመው ሁለቱም መሪዎች በቅርብ መተዋወቃቸው ነው፤ ለምሳሌ፣ መርኪና በ ገጽ 44 ላይ ስለ አማኑኤል ያሉትን እንመልከት፦

 

“አንድ ቀን የሚስዮኑ ኃላፊዎች፣ “በታንዛንያ ለሚካሄደው የሉተራን ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ስብሰባ የሲዳማን ቤተ ክርስቲያን ወክለህ እንድትገኝ ተጠርተሃል፣ ጉባኤው የሚካሄደው በክሊማንጃሮ ተራራ አጠገብ ነው” አሉኝ። እኔም ተደነቅሁና፣ “ከእነዚያ ታላላቅ ሰዎች ጋር ጉባኤውን ለመካፈል እኔ ምን ዕውቀትና ችሎታ አለኝ? የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ፣ ወደሚልከኝ ቦታ ሁሉ እሄዳለሁ” ብዬ “እሺ” አልኩኝ። ተነሥቼ የሚስዮኑ መሪዎች ጉባኤው ወደሚካሄድበት አገር ለመጓዝ ወደሚዘጋጅበት ወደ አዲስ አበባ ሄድኩኝ። ዶ/ር አማኑኤል አብርሃም እና ዶ/ር አማኑኤል ገ/ሥላሴ ከሚሄዱት መካከል ነበሩ። ለጉዞው ከመነሣታችን በፊት ዶ/ር አማኑኤል አብርሃም በመኖሪያ ቤታቸው የእራት ግብዣ አደረጉልን። በሕይወቴ እንደዚያ ዓይነት ግብዣ አይቼ አላውቅም። እሳቸው በጊዜው በኢትዮጵያ መንግሥት የተሾሙ ሚኒስትር ነበሩ። በድሆች መካከል ክርስቶስ ራሱን ዝቅ እንዳደረገ፣ እርሳቸው በእኛ መካከል ራሳቸውን ዝቅ ያደረጉ ነበሩ።”

 

ሁለቱም መጽሐፎች በድምሩ ቢያንስ የመቶ ዓመት የቤተክርስቲያንን ታሪክ ከነበረው ማሕበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ ይተረጉማሉ። ሁለቱም ጸሐፊዎች በሂደቶቹ ውስጥ ታዛቢ ብቻ ሳይሆኑ መሪዎችም ስለ ነበሩ ያቀረቡልንን ሠነድ ጠቃሚነት አጉልቶታል። በኛ አስተያየት ይህን መሰል መጽሐፎችን በቤተክርስቲያን አመራር ላይ የሚገኙ ሁሉ በጥንቃቄ ሊያነብቡ ይገባል። በመጽሐፍ ቅዱስ ትምሀርት ቤቶችና ሴሚናሪዎች እንደዚሁም የመሪነት ሥልጠና በሚሰጡባቸው ቦታዎች ሁሉ ዋነኛ የመማርያና የመወያያ መጽሐፎች ሆነው ሊቀርቡ ይገባል። የሁለቱን መሪዎች አመራር በጥንቃቄ መመርመር ተገቢም ጠቃሚም ነው። እነዚህን ዓይነት አገልጋዮች ስለ ሰጠን አምላካችንን በብዙ ልናመሰግነው ያስፈልጋል። በተጨማሪም አልተተረጎሙ እንደ ሆነ የአቶ አማኑኤል ወደ አማርኛ፣ የአቶ መርኪና ደግሞ ወደ እንግሊዝኛ ሊተረጎሙ ይገባል እንላለን። ጽሑፉን እንድናዳርስ ላስቻሉን ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳቸው። የመርኪ ታሪክ እነሆ፦

 

አቶ መርኪና መጃ ተወልደው ያደጉት በደቡባዊ ኢትዮጵያ በወላይታ ዞን ነው። የአቶ መርኪና አባት አቶ መጃ ማዴሮ በ 1888 ዓ.ም. ከአቶ ማዴሮ ሃናቆ እና ከወ/ሮ አሽሬ ዳኖሌ ተወለዱ። አቶ መጃ ነገሮችን ፈጥነው የመረዳት ችሎታ የነበራቸው አስተዋይ ሰው ስለ ነበሩ፣ ሰዎች ከቅርብና ከሩቅ እየመጡ የምክር አገልግሎትን ከእርሳቸው ያገኙ ነበር። መልካም ባሕርያቸውም በኅብረተሰቡ መካከል አክብሮትን እንዲያገኙ አድርጎአቸዋል።

 

አንድ ቀን አባቴ ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ብዙ ክፉ ሥራዎችን ይሠራ እንደ ነበር ነገረኝ፤ እኔም ክፉ ሥራ ሠርቼ እንደ ነበር ተገነዘብኩ። ወንጌል ወደ ማኅበረሰባችን ከመድረሱ በፊት በጨለማ ሕይወት ውስጥ እንኖር ስለ ነበረ፣ የተሻለው ነገር ምን እንደ ሆነ አናውቅም ነበረ። ከዚህም የተነሣ ሕይወታችን ጎስቋላና በፍርሃት የተሞላ ነበር። ከበሽታና ከሞት ለማምለጥ፣ አዝመራችን የበለጠ ምርት እንዲሰጠንና ሌላም ብዙ የሕይወት ውጣ ውረዶችን ለማለፍ መልካም መናፍስትንና ክፉ መናፍስትን መለማመን ነበረብን። ታላቅ እንደ መሆኔ መጠን፣ መሥዋዕት ለማቅረብ ከአባቴ ጋር የምሄደው እኔ ነበርኩ። በእኛ አካባቢ የታወቁ ሰዎች ወደ ፈለጉት አቅጣጫ አንድን ሰው አስከትለውና በቅሎ ላይ ተቀምጠው ይሄዱ ነበር። የአባቴን ካባ ተሸክሜ ከበቅሎአቸው ኋላ የምከተለው እኔ ነበርኩ። በእናቴ ቤተሰቦች በኩል አንድ ስሕተት ቢፈጸም ለመሥዋዕት የሚሆን በግ ይቀርባል። በአባቴ ቤተሰቦች በኩል ደግሞ ክፉ ሥራ ቢሠራ ወይፈን ይታረዳል። ከታረደው እንስሳ የተለያዩ ብልቶች ተወስደው ይጠበሱና ጠንቋዩ ይቀመጥ ባለበት ስፍራ ይቀመጣል። መስዋዕቱ ለሰይጣን የሚቀርብ ከሆነ ፍየል ይታረድና ሥጋው ጠንቋዩ ባዘዘበት ቦታ ይደረጋል። የበቆሎ እሸት እንደ ደረሰ ለዓመቱ ምስጋና የማቅረብ ሥርዓት ይካሄዳል። በቆሎውን ከነገለባው ጠብሶ ወይም ቀቅሎ በመንገድ ዳር ወይም ቤተሰብ ተሰብስቦ በሚያመልክበት ዛፍ ሥር ያኖሩታል። በተጨማሪም አባቴ ጣቶቹን በማር ውስጥ በማጥለቅና ወደ ሰማይ በመርጨት የጣዖት አምላክን ይለምን ነበር። የተረጨው ማር ተመልሶ ሲወድቅ ሮጬ ሄጄ ለመብላት እከጅላለሁ። ሆኖም አባቴ ያየኝ ይሆናል ብዬ እፈራ ስለ ነበር እተወዋለሁ።

 

በ1927 ዓ.ም. አንድ ቀን አባቴና እኔ ወደ ቤታችን ስንሄድ አረፋማውን ጅረት እየተከተልን ወደ ምንጩ አመራንና የአቶ አጌዶን ቤት ስናልፍ አቶ ዋንዳሮ ዳባሮ በአቶ አጌዶን ቤት ውስጥ ወንጌልን እየሰበኩ ኖሮ እኔና አባቴን አይተው ገብተን እንድንሰማ ጋበዙን። እኛም ተስማማን፣ ነገር ግን አባቴ እኔን በቅሎውን እንዳስር ሲያዝዘኝ ልጓሙን ፈትቼ እግሩን በገመድ በዛፍ ግንድ ላይ አሰርኩና ገብተን ለመስማት ተቀመጥን። አቶ ዋንዳሮ ስብከታቸውን ቀጠሉና በመካከሉም መዝሙር ጣልቃ እያስገቡ ያዘምሩ ነበር። ከመዝሙሮቹ አንዱ እንዲህ የሚል ነበር፦

     

በጎቹ የኢየሱስ ክርስቶስን ድምጽ ሲሰሙ

      ሊከተሉት ተፋጠኑ

      አስቀድመው ድምጹን ያልሰሙ ሊደርሱባቸው ተቻኮሉ

      እግዚአብሔርም ጠራቸውና ራሱን ገልጦላቸው ምሥጋናቸውን በደስታ ተቀበለ።

 

ሰባኪው ለረዥም ጊዜ ቢናገሩም እኔ የማስታውሰው ዋና ነጥብ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚች ዓለም አንድ ቀን ይመጣል የሚለውን ነበር። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። በእርሱ የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ይጥላቸዋል። “እናንተ ሰይጣንን ማምለክ አቁማችሁ በጌታ ኢየሱስ እመኑ። አለበለዚያ ግን ከሰይጣን ጋር ወደ እሳት ትጣላላችሁ። ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 209471 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:48

41849 comments

  • Comment Link iljarygzex Sunday, 19 May 2024 02:38 posted by iljarygzex

    Роза Ветров - цветочная мастерская, которая предлагает вам приобрести роскошные цветы. Ассортимент разнообразен, у нас найдете то, что вам нужно. Мы радуем своих клиентов доступными ценами и качественно собранными букетами. Быстро реагируем на заявки и с удовольствием готовы помочь вам с выбором. Заинтересованы в предоставлении вам лучших впечатлений. Ищете купить цветы в спб? Flowersspb.com - сайт, где есть возможность заказать с быстрой доставкой свежие цветы. Уверены в том, что получатели будут в восторге от сюрприза. Гарантируем отменное обслуживание, обращайтесь!

  • Comment Link Soanosbrern Sunday, 19 May 2024 02:04 posted by Soanosbrern

    На сайте https://t.me/mvavada ознакомьтесь с нужной, полезной информацией, которая касается уникального проекта «VAVADA». На официальном канале вы сможете ознакомиться со всей необходимой информацией. Здесь же представлены и актуальные промокоды, а также самые свежие и полезные новости, которые будут интересны всем, кто связан с игрой. Вавада предлагает ознакомиться с интересными, увлекательными играми, которые произведут на вас эффект. На этом канале, в первую очередь, появляются новости о таком заведении.

  • Comment Link Jaimekex Sunday, 19 May 2024 02:01 posted by Jaimekex

    See full T C page on 888casino. Winport Casino offers players a chance. Mobile Casino App Stars PA Online Casino Available Platforms iOS Apple App Store, Android Google Play, Desktop Web Browser App Store Listed As PokerStars Casino Real Money App Store Seller Stars Mobile Limited App Store Rating 4. Source: https://www.uwants.com/viewthread.php?tid=20525522

  • Comment Link NaavkAlasY Sunday, 19 May 2024 01:18 posted by NaavkAlasY

    Разработка электроники - компания, которая предлагает клиентам весь комплекс квалифицированных услуг. У нас можно сделать заказ на разработку электроники. Получите по телефону предварительную консультацию. Достаточный накопленный опыт дает возможность нам быстро включиться в проект. https://razrabotka.pro/ - сайт, где вы найдете осуществленные работы. Вы узнаете, как и кому, мы оказываем помощь. Также размещаем статьи, которые имеют отношение к изготовлению электроники и разработке. Свяжитесь с нами, будем рады обсудить детали вашего проекта.

  • Comment Link Kennethnoulp Sunday, 19 May 2024 01:15 posted by Kennethnoulp

    [url=https://redirect.m3ga.as]https m3ga gl[/url] - m3ga at, тор mega555net

  • Comment Link Larrysetty Sunday, 19 May 2024 01:14 posted by Larrysetty

    https KRAKEN - ссылка kraken, KRAKEN ссылка зеркало

  • Comment Link Hiramonery Sunday, 19 May 2024 01:03 posted by Hiramonery

    Wenn Sie ein Fan von Book of Ra sind, aber nach etwas Ähnlichem suchen, um Ihr Glück auszuprobieren, dann ist das Tipico Casino möglicherweise die perfekte Wahl für Sie. Das Tipico Casino bietet eine Vielzahl von Spielen, die dem beliebten Book of Ra ähneln und Ihnen ein ähnliches Spielerlebnis bieten können.

    Eines der Spiele, das dem Book of Ra sehr ähnlich ist, ist Book of Dead. Dieses Spiel wird von vielen Spielern als einer der besten Book of Ra-Klone angesehen und bietet ähnliche Funktionen und Gewinnmöglichkeiten. Mit aufregenden Bonusrunden und einer spannenden Spielatmosphäre ist Book of Dead ein echtes Highlight im Tipico Casino.

    Ein weiteres Spiel, das dem Book of Ra Г¤hnelt, ist Legacy of Dead. Auch dieses Spiel bietet Г¤hnliche Features wie das beliebte Book of Ra und sorgt fГјr jede Menge Spannung und Nervenkitzel. Mit tollen Gewinnchancen und interessanten Bonusfunktionen ist Legacy of Dead definitiv einen Spin wert.

    Das Tipico Casino bietet eine Vielzahl von Spielen, die dem Book of Ra ähneln und Ihnen ein aufregendes Spielerlebnis bieten können. Egal, ob Sie ein Fan von Book of Ra sind oder einfach nur nach etwas Neuem suchen, um Ihr Glück zu versuchen, im Tipico Casino werden Sie garantiert fündig. Probieren Sie die verschiedenen Book of Ra-ähnlichen Spiele aus und erleben Sie den Nervenkitzel des Glücksspiels auf eine neue Art und Weise. Viel Spaß beim Spielen!
    https://tipicocasino.one/

  • Comment Link Jamestrura Sunday, 19 May 2024 01:03 posted by Jamestrura

    Boomerang Casino Auszahlungsdauer

    Boomerang Casino ist ein beliebtes Online-Casino, das Spielern eine Vielzahl von Spielen und spannenden Aktionen bietet. Eines der wichtigsten Kriterien für Spieler bei der Auswahl eines Online-Casinos ist die Dauer, die eine Auszahlung benötigt. In diesem Artikel werden wir uns genauer mit der Auszahlungsdauer im Boomerang Casino befassen.

    Die Auszahlungsdauer im Boomerang Casino hängt von verschiedenen Faktoren ab, wie zum Beispiel der gewählten Auszahlungsmethode, dem Identitätsnachweis des Spielers und der Höhe des Auszahlungsbetrags. In der Regel bietet das Casino eine Vielzahl von Auszahlungsmethoden wie Kreditkarten, Banküberweisungen, E-Wallets und Cryptowährungen an, um Spielern eine schnelle und bequeme Auszahlung zu gewährleisten.

    Die durchschnittliche Auszahlungsdauer im Boomerang Casino beträgt in der Regel zwischen 1 und 5 Werktagen. Dies ist ein recht solider Zeitrahmen im Vergleich zu anderen Online-Casinos. Spieler sollten jedoch beachten, dass die Auszahlungsdauer je nach Auszahlungsmethode variieren kann. Zum Beispiel kann eine Auszahlung über eine E-Wallet wie Skrill oder Neteller schneller erfolgen als eine Auszahlung per Banküberweisung.

    Um die Auszahlungsdauer im Boomerang Casino zu minimieren, sollten Spieler sicherstellen, dass sie alle erforderlichen Dokumente zur Verifizierung ihrer Identität bereithalten und diese dem Casino schnellstmöglich zur Verfügung stellen. Dies kann dazu beitragen, Verzögerungen bei der Auszahlung zu vermeiden und den gesamten Prozess zu beschleunigen.

    Insgesamt bietet das Boomerang Casino seinen Spielern eine angemessene Auszahlungsdauer und eine Vielzahl von Auszahlungsmethoden, um sicherzustellen, dass Spieler ihre Gewinne schnell und bequem erhalten. Spieler sollten jedoch immer die jeweiligen Auszahlungsbedingungen und -zeiträume überprüfen, um sicherzustellen, dass sie gut informiert sind und keine unerwarteten Überraschungen erleben.
    https://boomerangcasino.one/

  • Comment Link Willieziday Sunday, 19 May 2024 01:03 posted by Willieziday

    Zet Casino: Kostenloser Bonus ohne Einzahlung

    Zet Casino ist eine beliebte Online-Glücksspielplattform, die Spielern eine Vielzahl von Spielen und Boni bietet. Einer der attraktivsten Boni, die das Casino seinen Spielern anbietet, ist der kostenlose Bonus ohne Einzahlung. Dieser Bonus ermöglicht es neuen Spielern, das Casino zu testen, ohne echtes Geld ausgeben zu müssen.

    Um den Bonus ohne Einzahlung bei Zet Casino zu erhalten, müssen sich neue Spieler lediglich auf der Website registrieren. Nach der Registrierung wird der Bonus automatisch gutgeschrieben und steht dem Spieler zur Verfügung, um verschiedene Spiele im Casino auszuprobieren. Dieser Bonus ermöglicht es Spielern, echtes Geld zu gewinnen, ohne selbst Geld zu riskieren.

    Der kostenlose Bonus ohne Einzahlung bei Zet Casino ist eine großartige Möglichkeit für Spieler, die Plattform kennenzulernen und erste Gewinne zu erzielen, ohne dabei ihr eigenes Geld zu verwenden. Es ist jedoch wichtig zu beachten, dass dieser Bonus bestimmten Umsatzbedingungen unterliegt, die vom Casino festgelegt werden.

    Insgesamt ist der kostenlose Bonus ohne Einzahlung bei Zet Casino eine hervorragende Möglichkeit für neue Spieler, um die Plattform zu erkunden und ihre Lieblingsspiele auszuprobieren, ohne finanzielle Risiken eingehen zu müssen. Spieler, die auf der Suche nach einem spannenden Online-Casino-Erlebnis sind, sollten Zet Casino definitiv eine Chance geben.
    https://zetcasino.one/

  • Comment Link Winstonanist Sunday, 19 May 2024 01:02 posted by Winstonanist

    Yes, you can win real money at Pennsylvania online casinos. All offers and events are subject to change or cancellation at management s discretion. 250 online casino games Fee-free payouts 24 7 phone email support. Source: https://forum.resmihat.kz/viewtopic.php?f=4&t=1946486

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.