በክፍል አንድ፣ ዲያብሎስን ለመቃወም እንዳንችል 1. ተናዝዘን ያልተውነው ኃጢአት 2. ማናቸውም ጥንቆላ ነክ (ዕቃዎችን) ወደ ቤት ማስገባት 3. ይቅር የማይል ልብ 4. ማንኛውም ክፉ ሃሳብ ያግደናል የሚሉ ነጥቦችን ወንድም ተድላ ሲማ ዘርዝሮልን ነበር። በዚህ ክፍል ደግሞ የቀሩትን አሳቦችና መፍትሔዎችን ያቀርብልናል።
መንፈሳዊ ዉጊያ [2]
ተድላ ሲማ
5. ሐዘንተኛ ልብ። ሁል ጊዜ የሚተክዝ ልብ ለሰይጣን ይመቻል። ቃሉ “ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ” ይላል (ፊል 4፡4)። የጌታ ደስታ ልባችንን ሊሞላው ይገባል። “የእግዚአብሔር ደስታ ኃይላችሁ ነውና (ነህምያ 8፡10)።” የእግዚአብሔር የሆነው ደስታ ወደ ልባችን ሲገባ ኃይልን እንሞላለን። ጌታ ኢየሱስ ወደ ምድር ከመጣባቸው ምክንያቶች አንዱ “በሐዘን መንፈስ ፋንታ የምስጋናን መጎናጸፊያ፤ በልቅሶ ፋንታ የደስታን ዘይት” (ኢሳ 61፡3) ሊሠጠን ነው። በመሆኑም ዘመናችንን ሁሉ በመተከዝ ዕድሜያችንን በሰይጣን ማስዘረፍ የለብንም። ሰይጣን ትናንት ስለ ሠራነው ስህተትና ስለ ደረሰብን ችግር፥ ዛሬ እያስተከዘ ዛሬን ይቀማናል። ይህ የጠላት ስልት ነው። ዛሬን ሳናጣጥም ነገ ይመጣብናል። ቃሉ “እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሴትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን” ይላል [መዝ (118):24]። አንድ ሰው እንዲህ አለ፣ “ዘጠና በመቶ ትኩረታችንን ማድረግ ያለብን በዛሬ ላይ ወይም ዛሬ ልንሠራቸው ባሰብናቸው ነገሮች ላይ ሊሆን ይገባል፤ አምስት በመቶ ደግሞ ስለ ትናንት በማሰብ ከስህተታችን ልንማር ከመልካም ተሞክሯችንም ልንበረታታ እንችላለን። አምስት በመቶ ደግሞ ስለ