×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:04

ያለ ዕውቀት መቅናት Featured

Rate this item
(0 votes)

የሚከተለው ርዕሰ አንቀጽ፣ ማኅበረ በኵር ካሳተመው፣ ከጮራ መጽሔት ቁጥር 34፣ ገጽ 1-2 ላይ የተወሰደ ሲሆን፣ ለብዙዎች እንዲዳረስ በማሰብ ለጥፈነዋል። ይህን ጽሑፍ ያዘጋጁትን ወገኖች እግዚአብሔር ይባርካቸው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፣ አሜን።

ያለ ዕውቀት መቅናት

ቅንአትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብሎ ለሁለት ከፍሎ ማየት የተለመደ ሆኗል። ሥጋዊ ቅናት በጥቅሉ ሲታይ፣ በሌላው ሰው ማደግና አንዳች ነገር ማግኘት ደስ አለ መሰኘትና የሌላው ይሆን ዘንድ ያልወደዱትን ለራስ ለማድረግ መፈለግ በመሆኑ ፍቺው ብዙም አያደናግርም። በመንፈሳዊ ስም የሚጠራው ቅናት ግን ሁል ጊዜ መንፈሳዊ ነው ለማለት ይቸግራል። እንዲያውም መንፈሳዊ ካባ የደረበ ሥጋዊ ቅናት ሆኖ የሚገለጥበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም።

እንዲህ ያለውን መንፈስ ለበስ ሥጋዊ ቅናት ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ‘ያለ ዕውቀት መቅናት’ ይለዋል። ይህን ያለውም የዘመዶቹን የአይሁድን ቅንአት ምንነት በገለጸበት ክፍል ነው። እነርሱ ለእግዚአብሔር የሚቀኑ መሆናቸውን ሐዋርያው አልሸሸገም፤ ለእግዚአብሔር የቀኑ ይሁኑ እንጂ፣ ቅንአታቸው በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተ የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆም በመፈለግ ለእግዚአብሔር ጽድቅ መገዛትን እንቢ አሉ [ሮሜ 10፣13]።

እንዲህ ባለው ቀናተኛነት ውስጥ ጳውሎስ የተባለው ሳውልም ዐልፏል። ለሙሴ ሕግ በመቅናት እግዚአብሔርን ያገለገለ እየመሰለው የክርስቶስን ተከታዮች በጽኑ ያሳድድ ነበር። በክርስቶስ ወደ ማመን ከተመለሰ በኋላ፣ በትዝታ ወደ ኋላ ተመልሶ በአይሁድ መካከል የሰጠው ምስክርነት ይህንኑ ያስረዳል። “እኔ … የአባቶቼንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፣ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ነኝ። ወንዶችንም ሴቶችንም እያሰርሁ ወደ ወኅኒም አሳልፌ እየሰጠሁ ይህን መንገድ [ክርስትናን] እስከ ሞት ድረስ አሳደድሁ” [የሐዋርያት ሥራ 22:3-4]። እንዲሁም ለፊልጵስዩስ ምእመናን በጻፈው መልእክቱ፣ “ስለ ቅንአት ብትጠይቁ፣ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤” ብሏል [3:6]። ምናልባትም ይህ በዘመኑ አይሁድ ዘንድ የቀናተኛነት ጣሪያ ተደርጎ ሳይወሰድ አልቀረም። ምክንያቱም ጳውሎስ ‘በቅንአትም ቢሆን እኔን የሚበልጥ ማንም የለም’ እያለ ነውና የሚናገረው [ቁ.4]። ይህ ሁሉ ግን፣ የሙሴ ሕግ የተሰጠው ፍጹም የሆነው [ወንጌል] እስኪመጣ ድረስ መሆኑን ካለማወቅ የመጣ ዐጕል ቅናት እንደ ሆነ ለመገንዘብ አያስቸግርም። ያለ ዕውቀት መቅናት ይሏል ይህ ነው።

ጳውሎስ ይህንና የመሳሰለውን ኢመንፈሳዊ ድርጊት ክርስትና ላይ ቆሞ ሲያስታውሰው፣ እንደ መልካም ሥራ ሳይሆን “እንደ ጕድፍ”፣ “እንደ ጕዳት”ም ነው የቆጠረው [ቁ.7-9]። ምክንያቱም ጌታ በወንጌል፣ “እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከምንም በላይ ደግሞ የሚገላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል” [ዮሐንስ 16:1-2] በማለቱ፣ እንዲህ ያለው ቅንአት፦ እግዚአብሔርን የሚያሳዝን እንጂ የማያስደስት ቅንአት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ክብርና ምስጋናን የሚያሰጥ ሳይሆን በኀጢአተኛነት የሚያስጠይቅና ኵነኔን የሚያስከትል ቅንአት፣ እንዲያው በጥቅሉ ባዶ ቅንአት መሆኑን አስተውሏል።

ዛሬም እንደ አይሁድ ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ የሚመላለሱ ሞልተዋል። በዘመናችን ለእናት ቤተ ክርስቲያን ህልውና ቀንተው የተነሡ ብዙዎች፣ ቅንአታቸውና ለቤተ ክርስቲያናቸው ያላቸው ፍቅር በራሱ ደስ የሚያሰኝ ነው ሊባል ቢችልም፣ ቅንአታቸውን የሚያሳዩበት መንገድ ግን በአብዛኛው ክርስቲያናዊናመንፈሳዊ ሆኖ አይታይም፤ በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተም ከአይሁድ ቅንአት የተለየ አይደለም።

ቅንአታቸው በእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት ላይ በተመሠረተ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚመራ አለ መሆኑ ዋናው መሠረታዊ ችግር ተደርጎ ይወሰዳል። ቤተ ክርስቲያንን እንደ አንድምድራዊት ድርጅት በመቍጠር፣ ህልውናዋን የእግዚአብሔርን ቃል በጥራት በማስተማር ሳይሆን በምድራዊ ጥበብና በሥጋዊ ኀይል ለማስጠበቅ ላይ ታች ይላሉ። የቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት በወንጌሉ ቃል ሳይሆን ማለቂያ በሌለው፣ የአሮጊቶችን ተረት በመሰለ ትምህርት እንዲሞላ ለማድረግ ይታገላሉ። ቤተ ክርስቲያን በቃለ እግዚአብሔር ወልዳ ያሳደገቻቸውንና ደረሱልኝ ብላ ተስፋ የጣለችባቸውን አገልጋዮቿን፣ ብርሃኑን ጨለማ፣ ጨለማውን ብርሃን፣ መልካሙን ክፉ፣ ክፉውን መልካም፣ ጣፋጩን መራራ፣ መራራውን ጣፋጭ [ኢሳይያስ 5:20] በማለት የተለያየ ስም እያወጡ ያሳድዳሉ። በሌሎች አስታከው ወንጌልንና የወንጌል እንብርት የሆነውን ኢየሱስን ይቃወማሉ። ውስጣዊ ዐይኖቻቸው በርተው እነዚህንና ሌሎችንም ክፉ ሥራዎቻቸውን፣ ለእግዚአብሔር በእውነት ቀንተው ስሙን ካስከበሩት እውነተኛ አገልጋዮቹ ሥራ ጋር ቢያስተያዩት ምንኛ ባፈሩ! ድርጊታቸውንም እንደ ጳውሎስ ጕዳትና ጕድፍ አድርገው በቆጠሩት ነበር።

ከመንፈሳዊ ቅንአት አንጻር፣ ከላይ ከተዘረዘሩት ክፉ ሥራዎች መካከል አንዱ ስንኳ ለእግዚአብሔር መቅናትን ማሳያ ሆኖ ሊጠቀስ አይችልም። ቤተ ክርስቲያን የገሃነም ደጆች የማይችሏት ሆኖ በክርስቶስ የተመሠረተች የእግዚአብሔር መንግሥት እንጂ፣ በሰዎች ስምምነት የተቋቋመች ምድራዊ ድርጅት ወይም “ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር” አይደለችምና ጠባቂዋ ራሱ ጌታ እግዚአብሔር መሆኑ በቅድሚያ መታወቅ አለበት። የሥልጣኗና የትምህርቷ መሠረት፣ የህልውናዋ መጠበቂያም ሌሎች የፈጠራ ጽሑፎች ሳይሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ምክንያት መሰደድ እንጂ ማሳደድ ከክርስቶስና ከሐዋርያቱ የተማረችው፣ የተቀበለችውም ግብሯ አይደለም። የወንጌልን ማእከላዊ መልእክት ክርስቶስን በመስበክ የምሥራቹን ቃል ታበሥራለች እንጂ፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ክርስቶስንና ወንጌሉን አትቃወምም።

አይሁድ ለሙሴ ሕግ ቀንተው ክርስቶስን በመስቀላቸው፣ ተከታዮቹ ሐዋርያትንም ተቃውመው እስከ ሞት ድረስ በማሳደዳቸው እግዚአብሔርን አሳዘኑት እንጂ ደስ አላሰኙትም። “እነርሱ ጌታ ኢየሱስንና ነቢያትን ገደሉ፤ እኛንም አሳደዱን፣ እግዚአብሔርንም ደስ አላሰኙትም፤ የሰውም ሁሉ ፀር ሆኑ፤ ይኸውም ይድኑ ዘንድ ለአሕዛብ እንዳንናገር ለመከልከል ነው፤ በዚህ ሁኔታ ኀጢአታቸውን ሁል ጊዜ በራሳቸው ላይ እስከ መጨረሻው እያከማቹ ይሄዳሉ። ቁጣውም በእነርሱ ላይ ያለ ልክ መጥቶአል” [1ኛ ተሰሎንቄ 2:15-16፤ ዐ.መ.ት.]። ስለዚህ በአይሁድ መንገድ ቀናተኛ የሆኑ ሁሉ፣ እንደ ጳውሎስ ጌታንና ቤተ ክርስቲያንን ከማሳደድ ተመልሰው ስለ ጌታ ስም ለመሰደድ ራሳቸውን ካላዘጋጁ፣ ስለ ገፉት የእግዚአብሔር ጽድቅና ስለ ፈጸሙት ኀጢአት፣ በዚህ ዓለም በተለያየ መከራና ችግር ይቀጣሉ፤ በመጨረሻው ቀንም ይጠየቁበታል።

ሰላም ሊሰጣት የመጣውን ጌታን በመቃወም ሰቅላ ለገደለችው፣ ወደ እርስዋም የተላኩ ነቢያትን ላሳደደችው ለኢየሩሳሌም በራሱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፣ “ኢየሩሳሌም፣ ኢየሩሳሌም ነቢያትን የምትገድል፣ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፉችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! [እናንተ ግን] አልወደዳችሁምም። እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል” [ማቴዎስ 23:37-38] ተብሎ እንደ ተነገረባት፣ በ 70 ዓ.ም. ሮማውያን አወደሟት፤ ብዙ አይሁድም ዐለቁ።

ዛሬም ያለ ዕውቀት “ቀናተኛ” የሆኑ ሁሉ፣ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከፈጸመችው ዐመፅና ዐመፅዋ ካስከተለባት ከዚህ ጥፋት መማር አለባቸው። ለእግዚአብሔር ቀንተናል በሚል እግዚአብሔርን ሲቃወሙ እንዳይገኙ ሊጠነቀቁ ይገባል። ለሰላማቸው የሚሆነውን የክርስቶስን ወንጌል መቃወማቸውንና የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምሯቸውን ማሳደዳቸውን የሚገፉበት ከሆነ ግን፣ የዘላለም ሕይወት እንዳይገባቸው በራሳቸው ላይ ፈርደዋል ማለት ነው [የሐዋርያት ሥራ 13:46]።

Read 460376 times

98636 comments

  • Comment Link Danielprele Sunday, 07 September 2025 23:30 posted by Danielprele

    узнать больше https://sosal-vodkabet.io

  • Comment Link MartyMoulk Sunday, 07 September 2025 23:29 posted by MartyMoulk

    learn the facts here now
    aviator

  • Comment Link Richarddum Sunday, 07 September 2025 23:24 posted by Richarddum

    check this https://toast-wallet.io

  • Comment Link pasaran cambodia Sunday, 07 September 2025 23:18 posted by pasaran cambodia

    It's the best time to make some plans for the future and it is time to be
    happy. I have read this post and if I could I wish to suggest you few interesting things or
    advice. Perhaps you could write next articles referring to this article.

    I want to read even more things about it!

  • Comment Link Robertsof Sunday, 07 September 2025 23:12 posted by Robertsof

    подробнее
    vodkabet водка бет казино

  • Comment Link Danielexhap Sunday, 07 September 2025 22:37 posted by Danielexhap

    her latest blog Xrp wallet

  • Comment Link Robertsof Sunday, 07 September 2025 21:57 posted by Robertsof

    Читать далее
    водка бет

  • Comment Link Davidtef Sunday, 07 September 2025 21:06 posted by Davidtef

    в этом разделе https://vodkabet.kz/

  • Comment Link muelear oxidize parteurize Sunday, 07 September 2025 20:46 posted by muelear oxidize parteurize

    Wonderful goods from you, man. I've understand your stuff previous to
    and you're just too magnificent. I really like what you've acquired here, certainly like what you are saying
    and the way in which you say it. You make it enjoyable and you
    still care for to keep it smart. I can't wait to read far more from you.
    This is really a terrific site.

  • Comment Link 789bet Việt Nam Sunday, 07 September 2025 20:46 posted by 789bet Việt Nam

    You could certainly see your enthusiasm within the work you
    write. The world hopes for more passionate writers like you who aren't afraid
    to say how they believe. All the time follow your
    heart.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.