×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:07

ፖለቲካና ሃይማኖት ይቀላቀላሉ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ርዕሰአንቀጽ - ልዩ እትም

ፖለቲካና ሃይማኖት ይቀላቀላሉ

ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም ይባላል እንጂ ተነጣጥለው አያውቁም። ሰው ማህበራዊ ፍጡር ነው፤ ፖለቲካም በጋርዮሽ  የሚከናወን የሥልጣን ግንኙነትና አደረጃጀት ነው። ሰው ሃይማኖተኛም ነው፤ ራሱን ወይም ከእርሱ ውጭ ያለን ያመልካል፤ አምላክ የለም በማለቱ አምላኪነቱን ያውጃል። ለነፍሱ ያደረ ፈጣሪውን ያመልካል፤ ለአብዮት ያደረ አብዮት ያመልካል፤ ለሥጋው ያደረ ሥጋና ዓለምን ያመልካል።

ከዕለታት አንድ ቀን በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ሃይማኖትና መንግሥት ተደጋግፈው በሰላም ይኖሩ ነበር። “ሃይማኖት የግል፣ አገር የጋራ ነው” መርሕ ነበር። በደርግ ዘመን ሃይማኖት ተወገዘ፤ እግዚአብሔር በአዋጅ ታገደ። የምሥራቃውያን ዐመል ብቅ አለ። ወደ ምሥራቅ ተዞረ። መንግሥት ካዘዘልህ ውጭ ወዮልህ መጣ። “እግዚአብሔር ይመስገን” ተከለከለ።

እንደምን አደርክ?

ደህና፣

ቤተሰብ እንዴት ነው?

ደህና፣

ሥራ እንዴት ነው?

ደህና።

አንድ ፈረንሣይ ለጋሲዮን የሚኖሩ ወይዘሮ፣ “እግዚአብሔር ይመስገን” ማለት ስላበዙ፣ ካድሬው በልግጫ፣ “ሴትዮ፣ እግዚአብሔር የሚባል የለም፤ ምን እግዚአብሔር እግዚአብሔር ትያለሽ?” ቢላቸው፣ የማይበገሩ ሴትዮ፣ “ከቤቴ ስወጣ አነጋግሬው የመጣሁትን እንዴት የለም ትለኛለህ?” ብለው አፍ አስይዘዋል።

በሶቭየት መጤ ሃይማኖት አገር ተወረረች። ደም ፈሰሰ፣ መንግሥትና ሃይማኖት ተፋቱ ተባለ። ለፖለቲካ ስላላመቸ ቆይቶ “ሃይማኖት አይለያየንም” መጣ። ወሬው “እኩልነት” “ነፃነት” ሆነ። የመስቀል አደባባይ ፕሮቶኮሉ ተቀየረ፤ ከሊቀመንበሩ በስተቀኝ የቤተክህነት መሪ፣ በስተግራ የመስጊዱ ተሰየሙ። የግል የሚባል ለጊዜው ከሠረ። “ሃይማኖት ለፖለቲካ፣ ፖለቲካ ለሃይማኖት” የሚል ስልት ተቀየሰ። “የየሱስ ቃል አያረጅም” የምትለዋ የስዩም ገብረየስ ዝማሬ በአብዮት ሐዋርያት ተጠልፋ የወቅቱን ረብሻ በጉያዋ ደብቃ ብቅ አለች።

በ1983 ዲሞክራሲ የሚሉት ከምዕራቡ ዓለም ከገንዘብ እርዳታ ጋር ተላከልን። እኛም የምዕራባውያንን ዐመል ተቀበልን። ዲሞክራሲም ግለኛነትን እያገነነ “እኔ እኔ፣ ለኔ ለኔ” እያለ ቁና እየተነፈሰ ደረሰ። ወደ ምዕራብ ተዞረ! “ሃይማኖት የግል ነው” በየግልህ ተባለ። በየቀዬህ በየክልልህ ዛፍ ቢሆን ጥላህን ማምለክ መብትህ ነው ተባለ። የእኩልነትና የነፃነት መጽሐፍ ተደገመ።

በአፄ ኃይለሥላሴና በደርግ፣ እንደ ዘመነ ዲሞክራሲ መምረጥና መመረጥ አልነበረም። ሥልጣን፦ መስሎ ላደረ ሹመት፣ ለተዳፈረና ላቅማማ ሽረት ግዞትና ሞት ነበረ። በቀድሞው ልክ ባይሆንም ዛሬም ይኸ አልጠፋም። አሁን ግን ዲሞክራሲ ተብሏልና መምረጥና መመረጥ የሚለው አሠራር ገበያ ላይ ወጥቶ ፀሐይ እየሞቀ ነው። እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ልዩነቱ። ሰው ያለ ተጽዕኖ መምረጥ ከቻለ ስብዕናው ተከበረ፣ ሕልውናው ተዘከረ ማለት ነው። መሪነት ብቃት ላላቸው ሁሉ እንጂ ለጥቂቶች የተሰጠ መብት አይሆንም። ወይም መሪዎች እንድ ግብጽ አማልክት ለዘላለም ተሰይመው ሕዝብ የሚያንቀጠቅጡበት አይሆንም፤ ስለ ታታሪነታቸው፣ የሕዝብ አገልጋይና አደራ ተሸካሚ ስለ መሆናቸው ተጠይቀው ግልጽ መልስ የሚሰጡበት፣ የሚመረጡበት ወይም የሚሻሩበት ሁኔታ የተፈጠረበት ዘመን ነው። ሃይማኖተኞችን በምጸት፦ እዚህ ምን ታደርጋላችሁ? ሄዳችሁ ብትጸልዩ አይሻልም? ሲሉ የነበረ እንዲመረጡ ደጅ ጥናት ከጀመሩ ሰነበተ። ተረስቶ የኖረ ሕዝብ በተፈላጊነቱ ሲኩራራና ሲሽኮረመም ማየት ተስፋ ሰጭ ነው። ቅንጅት በ1997 ምርጫ ዋዜማ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲጸልይ ማሳሰቡ ሃይማኖተኞችን ማግባባቱ ነበር። የቀድሞው የደርግ መሪ በቀውጢ ሰዓት ክርስቲያኑና እስላሙ በየቤተ አምልኮው አምላኩን እንዲማጸን መማጸናቸው አይረሳንም። የደረሰባቸው ጭንቅ ቀድሞ የተናገሩትን ሁሉ አስረስቶአቸው። ለሶሻሊስት ጓዶቻቸው ግን ይህን የነገሩ አይመስለንም፤ ምክንያቱም ቅድም እንዳመለከትነው እግዚአብሔር ስለሌለ ለማን ይጸልዩ? [እርግጥ ጓዶቹ በየጓዳቸው ጸልየው እንደ ሆነ ማወቅ አንችልም፤ ይህንን የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው]።

የትላንቱ ፖለቲከኛ ሞት ሳይጠራ [“እናት አገር ወይም ሞት!”] ወይም ሰማይና ምድርን ሳይራገም [ይውደም! ይውደም!] ንግግሩን አይቆርጥም። የዛሬ ዘመን ፖለቲከኛ ግን ዋዛ አይደለም። በየንግግሩ መሃል የእግዚአብሔርን ስም ጣልቃ እያስገባ [ሲመችም ለሙስና እየሰገደ] ያሳርጋል። ከአሜሪካ ፖለቲከኞች ቀድቶ ይሆን? እየቆየ እየቆየ የሚገርም ነገር አይጠፋም። እግዚአብሔርም ተቸገረ እኮ! የሶቭየት ሃይማኖት አገራችን ሲገባ “እግዚአብሔር የለም፣ አገር ለቆ ሄዷል” እንዳልተባልን፤ መንግሥታት ሲንኮታኮቱ ከወደ አሜሪካ ብቅ ብሎ ይሆን? የኛዎቹስ አሥሬ እግዚአብሔርን የሚጣሩ በአዲስ አበባና በዋነኛ ከተሞች የሞላውን የወንጌል አማንያንን ድምጽ ለማግኘት አለማቀዳቸውን ማስተባበል አይቻልም። በአንጻሩ ሃይማኖት ማጥላሊያና ተቀናቃኙን ለማጣጣያ ፍቱን መሣሪያ ሆኗል። ደግማ እሥር ቤት የወረደችው ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ አንድ ሰሞን “ጴንጤ” ነች መባሉ ለሙገሳ ወይም ስለርሷ ሐቁን ለመናገር ሳይሆን ለማዋረድ እንደ ነበር የሚያጠያይቅ አይደለም። ምክንያቱም “ሃይማኖት የግል ነው” ሲባል የሰማነው ድሮውንም ከልብ አልነበረማ።

ከዓመት በፊት የተፈቱት የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር የአቶ ታምራት ላይኔ ጉዳይ ሌላኛው ነው። በሙስና ተከሰው ከ 12 ዓመት እሥራት በኋላ በአመክሮ ሲፈቱ በአደባባይ “ፖለቲካ በቃኝ፣ ከእንግዲህ ኢየሱስን አገለግላለሁ” ማለታቸው ብዙ ጥያቄና ወረፋ አድርሶባቸዋል። [“ሙስና”፣ ጥንት “ጉቦ” የምንላት ነች፣ ዛሬ ቀጭን ነጠላ ደርባ ብቅ አለች። ደርግ “መንፈስ” ሲል ረቂቅ ቁሳዊነትን ለመግለጽ እንጂ ከቁስ ውጭ እውነት አለ ማለቱ እንዳልነበረ ሁሉ።] ታዲያ አቶ ታምራት ፖለቲካ በቃኝ ማለታቸው ምናኔም እንደማያስጥላቸው የዘነጉ አይመስለንም። “አለም አቀፍ ፈውስ በፍቅርና በአንድነት” ብለው የጀመሩት “ሚኒስትሪ” ሌላው ቢቀር የፖለቲካ ሂደቶችን ማጤንና ከፖለቲካ መሪዎች ጋር መግባባትን እንደሚጠይቅ አይታጣቸውም። በየሄዱበት “የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር” መባላቸው የፖለቲካ ጠባሳ እንደተወ የማይገነዘቡ አይመስለንም። እሰብካለሁ ያሉት ወንጌል፣ ሥር ነቀል ለውጥ የሚያስከትል በመሆኑ ምናልባት ዳግም “ሙስና” ውስጥ አልገኝም፣ ከሚያባልግ ሥልጣን እቆጠባለሁ ማለታቸው ይሆናል። ወይም ክርስቶስ ይቅር ብሎኛል እኔም እንደ ዘኬዎስ ማህበራዊ በደሌን አስተካክላለሁ፣ አካክሳለሁ ማለታቸው ይሆናል [ሉቃስ19፡1-10]። ክርስቶስን ሳያውቁ የኖሩትን  ሕይወት ባዶነት ከተረዱስ፣ ኢየሱስ ሕያውና እውነተኛ ጌታ እንደ ሆነ ካመኑ፣ ያለፉበትን የትግልና የሥልጣን ዘመን ከቀመሱት አዲስ ሕይወት አንጻር እውነቱን በመጽሐፍ የማስፈር ብሔራዊ፣ ሰብአዊና የታሪክ ግዴታ እንዳለባቸው እናሳስባለን። ለማንኛውም አንድ ጸሐፊ ወደ ክርስቶስ ማህበር መቀላቀላቸውን አስመልክቶ “ፖለቲከኛ ሲያረጅ፣ ሰባኪ ይሆናል” ብሎ  በከረመ ቁጣና በጥርጣሬ ተችቶአቸዋል። እግዚአብሔርን ማሰብ በስተርጅና ወደ ሞት መቃረቢያ ላይ ነው ማለቱ ይሆን? ምስክርነታቸውን ልብ ብሎ ለሰማ ግን ወንድም ታምራት እውነተኛ የሕይወት ለውጥ እንዳገኙ አያጠራጥርም። የቀረውን ጊዜ ይገልጠዋል። የጠቀስነው ጸሐፊ የክርስቶስን ወንጌል ኃይልና ምሥጢር ካለማወቅ የተነሳ እዚህ ድምዳሜ ላይ ደርሶ ይሆናል ብለን አልፈነዋል።

በሚያዝያ ወር ላይ ከላሊበላ ወሎ ተመራጭ የሆኑት ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው “ጴንጤ” ሆኑ ተብሎ አገር ታመሰ። “ብሮስታንት” ወይም “ጴንጤ” ሆኑ ብለው ያሟቸው ምን ማለታቸው እንደ ሆነ አላብራሩም። ይኸ “ብሮስታንትና ጴንጤ” በደፈናው መኾን የሌለበት፣ እንደ ለምጥ የሚሸሽ ነገር ይመስላል። “ጴንጤ” ሲፈለግ ማስፈራርያ ሲፈለግም ማግባብያ ነው። አቶ ልደቱን፦ “ጴንጤ ነዎት ይባላል፣ ጴንጤ ነዎት?” ሳይሆን “በኢየሱስ ክርስቶስ ያምናሉ?” ማለት ልኩ ነበር። ለማለት አልን እንጂ ስለ ልኩ የሚገደው ማን ነው? እርሳቸውም ሲመልሱ፣ ስሜን ለማጥፋት ባላንጣ የነዛብኝ እንጂ እኔስ “ጴንጤ” አይደለሁም፣ ሃይማኖቴን አልለወጥኩም እያሉ ነው። ቀድሞውኑ የያዙት ክርስቶስን ከሆነ ሃይማኖታቸውን አጸኑ እንጂ አልለወጡም። ታሪክ ራሱን ይደግማል። አፄ ኃይለሥላሴም እንደዚሁ የወሎውን ልጅ ኢያሱን ሰለሙ ብለው በቤተክህነት ትብብር ሕዝብ እንዳስነሱባቸው ታሪክ ነግሮናል። መቸ ይሆን የሃይማኖት መሪዎች ለኑሮአቸውና ለሥልጣን ሲሉ ከምድራዊ ሥልጣናት ጋር መመሳጠር የሚያቆሙ? የፖለቲካ መሪዎችስ መቸ ይሆን ሳይጦሙ ጦም ማወጅ የሚያቆሙ?

ለመሆኑ፣ ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም የሚለው አስተሳሰብ ከወዴት መጣ? በመጀመሪያ ፖለቲካ ምን እንደ ሆነ ካለማወቅ ነው። ወይም በተሳሳተ መንገድ ከመረዳት ነው። ፖለቲካ መጥፎ፣ ቅጥፈት የሞላበት ጉዳይ ነው ከማለት፤ [ይህም በአንድ መልኩ ትክክል ነው።] ለነፍሱ ያደረና ወንጌል ያነበበ ሰው ከእንደዚህ ዓይነት ምግባር መራቅ  ይኖርበታል ከማለት። ፓለቲካ ግን ከላይ እንደ ጠቀስነው በቅድመ አሳቡ የመንግሥት ሥርዓትና አስተዳደር ነው፤ በክፉዎች እጅ ለክፉ፣ በቅኖች እጅ ለበጎ ሊውል ይችላል። ቀጥሎ፣ የሃይማኖትን ምንነት ካለመረዳት ነው። ሃይማኖት ሲባል ለሰማይ መንግሥት መዘጋጃ ሥጋን ለማጎሳቆያ እንጂ የምድሩን ለመመርመሪያና ታግሎ ኑሮን ለማሸነፊያ እንዳልሆነ ይታሰባል። ይኸ ነው አብዮተኛውን ትውልድ ዙሪያ ገባውን የነገሠውን ድህነት፣ ድንቁርናና የፍትሕ መጓደል አይቶ ሃይማኖትን ለመጥላትና ቤተክርስቲያንን ለማሳደድ ያነሳሳው። እንግዲህ ፖለቲካዬን የሚል ፖለቲካው ውስጥ ይገባል፤ ሃይማኖቴን የሚል ደግሞ እንደየሃይማኖቱ ይሆናል ማለት ይመስላል። ሃይማኖተኛ ትርፍ ሲያይ ፖለቲካውን ይያያዘዋል። ፖለቲከኛም ሲከስር ወይም መከራ ሲበዛበት ሃይማኖተኛ ይሆናል። በዚህ ስሌት ሁለቱ እንደ ዘይትና ውሃ ናቸው፣ አይቀላቀሉም፤ ፖለቲካም እንደ ኮሬንቲ ነው፣ አይቀረብም።

ወንጌል ግን ምን ይላል? ላመኑ “የምድር ጨው ናችሁ” ይላቸዋል። ማህበረሰብ የሞራል ቅንቅን ቦርቡሮ እንዳያፈርሰው ተሳትፎአችሁ አስፈላጊ ነው ይላል። “የዓለም ብርሃን ናችሁ” ይላል። ዓለም ጨለማ ነች፤ እውነትን ከሐሰት መለየት እንዳይጠፋ ብርሃን የሆነውን፣ ጻድቅ ፈራጅ የሆነውን፣ የሰላም አለቃ የሆነውን ኢየሱስን ለማወጅ ታስፈልጋላችሁ። ፈርሃ እግዚአብሔር ሠርጾ እንዲወጣ ምልክት ናችሁ ይላል። ለመሪዎች ጸልዩ፣ ፍትሕ እንዳያጓድሉ፤ በአምላክ አምሳል የተፈጠረውን እንዳይንቁ እንዳያጠቁ፣ ምድርን እንዳያራቁቱ፣ ራሳቸውን እንዳያተልቁ። “ክንዳችን ይህን ሠራችልን” እንዳይሉ።

         

ግንቦት 15/2002 የሕዝብ ምርጫ ይደረጋል። ክርስቲያኖችም እንደ ተቀረው ሕዝብ ብሔራዊ ግዳጃቸውን ሊወጡ፣ መብታቸውን ሊያስከብሩ ድምጽ በመስጠትና በመቀበል በምርጫው ይሳተፋሉ። ከዚህ አንጻር ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም የሚለው አባባል የተሳሳተ ብቻ ሳይሆን ጎጂ ነው። ግብር መክፈል ፖለቲካ ነው። በጎ አድራጎት ፖለቲካ ነው። መገኘት ራሱ ፖለቲካ ነው። “ኢየሱስ በሁሉም ላይ ጌታ ነው” ማለት ከፖለቲካም ዋና ፖለቲካ ነው። ከዳር የቆምን በመሰሉን ዘመናት ሁሉ የፖለቲካው ተካፋይ እንደ ነበርን መካድ አንችልም። መፈክሩ፣ “ከሁሉም በላይ አብዮቱ” ሲለን፣ የለም ምን ተደርጎ፣

“ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው

በምድር በሰማይ”

ያልናቸው ጊዜአት ዛሬም አልተለወጡም። ይኸ በነፍሳችን ተወራርደን የምንኖረው ኑሮ ነው። ሃይማኖትና ፖለቲካ አይነጣጠሉም ስንል ግን ከመንግሥት አስተዳደር አንጻር አባባሉን ልናርም ይገባል። የአንድ አገር ሕዝቦች እምነታቸው አንድ ወጥ ስላይደለ፣ ቅድም እንደጠቀስነው ሰው ክቡርነቱ በጅምላ ሳይሆን በግል በፈጣሪው አምሳል መፈጠሩ ስለሆነ፣ የሃይማኖትና የመንግሥት አደረጃጀትና ተልዕኮ ሊነጣጠሉ ያስፈልጋል። ቤተክርስቲያን ኃይሏና ሥልጣኗ ለግራና ለቀኝ የማይለውን ለነፍስና ለሥጋ ለውጥና ተስፋ የሚያመጣውን ወንጌል ስትሰብክ ነው። የዜጎች እምነት የተለያየ ስለሚሆን የዜግነት መብታቸው ሊጣስ አይገባም። ይህን እንጂ ያንን አምኖ ላለመከተል ነፃነት ሊኖር ይገባል። ሃይማኖቱን በግፊት ሳይሆን በአክብሮት የመለፈፍ መብቱ ሊከበርለት ይገባል። ሃይማኖትና መንግሥት አይደራረሱ ማለት አይቻልም። ሳውዲ በሕግ የእስላም አገር ናት፣ ክርስቲያን መሆን በልምድ እንዳየነው እንደ መብት አይቆጠርም፤ ብዙ አሣር ያስከትላል። ዛምቢያ በሕገ መንግሥት የክርስቲያን አገር ናት፤ እስላም መሆን ግን ለእስር አይዳርግም፤ ዜግነትን አያስነጥቅም። የተቀሩት አገሮች ይህንኑ በተለያየ መልኩ ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ። ባጭሩ፣ ሙስሊሞች በክርስቲያን አገር ያላቸውን ነጻነት፣ ክርስቲያኖች በሙስሊም አገር አይኖራቸውም።

እፊታችን ባለው ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ምን ጠቃሚ ክርስቲያናዊ መመዘኛዎች ሊኖሩ ይችላሉ? እንግዲህ ዝርዝሩ ላይ አቋማችን ሊለያይ ቢችልም፣ መሠረታዊው ላይ አንድ ነው። መሠረታዊው ምንድነው? የመጀመሪያው፣ የሥልጣን ሁሉ ምንጭና ባለቤት እግዚአብሔር ነው። ቢገነዘቡ ባይገነዘቡ ሥልጣን ላይ ያሉ ሁሉ ሥልጣናቸው በአደራ የተሰጣቸው ነው። መሪዎች የሚሾሙት ጽድቅና ፍትሕን ለማስፈን ነው። በምድሪቱ ሰላም ቢሆን ከእግዚአብሔር ነው፣ የአማንያን ጸሎትና ተሳትፎ ፍሬ ነው። ስደትና መከራ ቢመጣ እግዚአብሔር ለዓላማ ፈቅዶ ነው። ሁሉን የሠራ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በሠራው ሰው ሊመሰገን አይገባም። ወንጌልን ያመኑ በሞት ሆነ በሕይወት ከእግዚአብሔር ሌላ ተጨማሪ ምክንያት አያሻቸውም።[ፊል1፡20] አለዚያ በሰላሙ ሰዓት ሰውን ማመስገን፣ በስደት ደግሞ እግዚአብሔርን ማማረር ሊመጣ ነው። ሁለተኛው፣ ሰው ሁሉ በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥሯል የሚል ነው። [1ኛቆሮ11፡7፤ዘፍ1፡27] ሰው ከዝንጀሮ መጣ ወይም ክብሩና ህልውናው የተቃረኑ ማህበራዊ ኃይላት ውጤት ነው የሚል ሁሉ የሳተ ነው። ወይም አንዱን ሰው ወይም ጎሣ ከሌላው ሰው ወይም ጎሣ የሚያበላልጥና የሚያቃቅር አስተሳሰብ ሁሉ የወንጌልን ሥልጣን የሚጻረር ነው። ሦስተኛው ከሁለተኛው የሚቀጥል ነው፤ ይኸውም፣ ሰው በአምላክ አምሳል ተፈጥሯል ካልን፣ የደሆች [የሥራ አጦች፣ የአዛውንት፣ የመንገድ ተዳዳሪ ሕጻናትና ሴቶች] ሁኔታ ምን ይመስላል? መሪዎች የገቡትን ቃል ያጥፋሉ ወይስ ይፈጽማሉ? ሕግ ለሁሉም እኩል ይሠራል? ሰብአዊ መብት [የመደራጀት፣ የመናገርና የመጻፍ] ይከበራል? ክፉ የሚያደርጉ ተመስግነው መልካም የሚያደርጉ ይገፋሉ? በዚህ ሁሉ ቤተ/ክ ምዕመኑን በጽድቅ ወንጌል ማስታጠቅ ትታ ከምድራዊና ጊዜአዊ ድርጅቶችና አስተሳሰቦች ጋር መወዳጀትና መወገን ብትጀምር ሥልጣኗን ትጥላለች፤ ያም ለክርስቶስ ክብር አይሆንም። ጸጋ፣ ችሎታና ጥሪ ያላቸው አማንያን ደግሞ ተመርጠው በፖለቲካም መሳተፍ ይችላሉ።

ከሁሉ በላይ ግን መጸለይ ነው፤ ሰላም እንዲኖር፣ አመጸኞች እንዲገቱ፣ እንዳያይሉ፣ የሰላም ሰዎች፣ ቅን ዜጎች፣ ፍትሕ የሚወዱ እንዲነሱ። ባለጠጎች ደሃውን መኖሪያ እንዳያሳጡት። የተሰጠን የክርስቶስ መንፈስ ስለሆነ እርሱ ወደ እውነት ሁሉ ይመራናል። ሰው የማያየውን ያያል፤ ፖለቲካ የማይመረምረውን ይመረምራል። የእግዚአብሔር መንፈስ ሰው እንደሚያይ አያይም። ሥልጣናትና ኃይላት በስውር የሚመክሩትን ይሰማል፣ ለባሪያዎቹ ያስታውቃል። ቅንነት የተገኘበትን ይገነዘባል፤ መነሻን ብቻ ሳይሆን ፍጻሜን ያያል። ከስምንቱ የእሴይ ልጆች በነቢዩ ሳሙኤል የተመረጠው በሥፍራው ላይ ያልነበረው ትንሹ ዳዊት ነው። እግዚአብሔር እንደ ቂሮስ ያሉትን አሕዛብ ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ያስነሳል። ይህን ያነሳል፤ ያንን ይጥላል። ዕጣ በጉያ ይጣላል፣ መደብዋ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር የእግዚአብሔርና የመሲሑ ነው። እግዚአብሔር ምድራችንን ርህራሄ፣ ቅንነትና ማስተዋል ባላቸው ሰዎች ይባርክልን። [ጥቅሶች፦ ሮሜ 13፡1-5፤ የሐዋ ሥራ 5፡29፤ ራእይ 13፤ 1ኛጴጥሮስ 2፡13-17፤ ማርቆስ 12፡13-17፤ ቲቶ3፡1፤ ምሳሌ16፡33፤ 1ኛሳሙኤል16፤ 2ኛነገሥት 6፡8-13፤ 2ኛ ዜና 36፡22፤ ዕዝራ1፡2፤ ኢሳይያስ 6፡1-]               5/13/2010

 

Read 618924 times

147509 comments

  • Comment Link bbs.dnmso.com Friday, 04 February 2022 08:33 posted by bbs.dnmso.com

    Hello are using Wordpress for your site platform? I'm new to the blog world but I'm trying to get started and set
    up my own. Do you require any coding knowledge to make your
    own blog? Any help would be greatly appreciated!

  • Comment Link phonographic.science Friday, 04 February 2022 08:33 posted by phonographic.science

    I was curious if you ever thought of changing the
    layout of your site? Its very well written; I love what youve got to say.
    But maybe you could a little more in the way
    of content so people could connect with it better.
    Youve got an awful lot of text for only having 1 or two pictures.

    Maybe you could space it out better?

  • Comment Link ai-db.science Friday, 04 February 2022 08:32 posted by ai-db.science

    Good post. I'm experiencing a few of these issues as well..

  • Comment Link www.cakeresume.com Friday, 04 February 2022 08:32 posted by www.cakeresume.com

    Hello, everything is going nicely here and ofcourse every one is sharing information, that's truly fine, keep up writing.

  • Comment Link https://cutt.ly/1Om2pX6 Friday, 04 February 2022 08:32 posted by https://cutt.ly/1Om2pX6

    Hi colleagues, how is everything, and what you wish for to say concerning
    this piece of writing, in my view its truly awesome for me.

  • Comment Link https://notes.io/PZpP Friday, 04 February 2022 08:30 posted by https://notes.io/PZpP

    Spot on with this write-up, I truly think this web site needs a
    lot more attention. I'll probably be returning to see more, thanks for the advice!

  • Comment Link http://driverpoisk.ru/index.php?qa=userqa_1=felonyracing9 Friday, 04 February 2022 08:30 posted by http://driverpoisk.ru/index.php?qa=userqa_1=felonyracing9

    Great blog! Do you have any recommendations for aspiring writers?

    I'm hoping to start my own site soon but I'm a little lost on everything.
    Would you propose starting with a free platform like
    Wordpress or go for a paid option? There are so many choices out there that I'm totally
    confused .. Any recommendations? Cheers!

  • Comment Link https://v.gd/O6dYfN Friday, 04 February 2022 08:29 posted by https://v.gd/O6dYfN

    Thank you a lot for sharing this with all people
    you really understand what you're speaking approximately!
    Bookmarked. Please additionally talk over with my web site =).
    We will have a hyperlink exchange agreement between us

  • Comment Link menwiki.men Friday, 04 February 2022 08:28 posted by menwiki.men

    Hmm is anyone else experiencing problems with the pictures on this
    blog loading? I'm trying to find out if its a problem on my end or if
    it's the blog. Any responses would be greatly appreciated.

  • Comment Link https://timeoftheworld.date/wiki/Minecraft_Install_Secrets_That_No_One_Else_Knows_About Friday, 04 February 2022 08:27 posted by https://timeoftheworld.date/wiki/Minecraft_Install_Secrets_That_No_One_Else_Knows_About

    I absolutely love your blog and find the majority of your post's
    to be just what I'm looking for. can you offer guest writers to write content for
    you? I wouldn't mind creating a post or elaborating on a number of the subjects you write in relation to here.
    Again, awesome web log!

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.