×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:09

መሬት መሬት ሲያይ Featured

Rate this item
(0 votes)

ርዕሰ አንቀጽ

መሬት መሬት ሲያይ

አምስት ብር መንገድ ላይ ወድቆ ያገኘ አንድ ወጣት፣ ሌላም አገኝ እንደሆን ብሎ መሬት መሬቱን ሲያይ ረጅም ዓመታት አሳለፈ። በዓመታቱ መካከል ይኸው ወጣት ብዙ ነገር ለቃቀመ። ሃያ ዘጠኝ ሺህ አምስት መቶ አሥራ ስድስት አዝራሮችን፣ ሃምሳ አራት ሺህ አንድ መቶ ሰባ ሁለት የማስታወቂያ መርፌ ቁልፎችን እና አሥራ ሁለት ሳንቲም ለቀመ። ወፍራም መቀነት የማያስታግሰው የወገብ ህመምና ንፉግነትን አተረፈ። መሬት መሬት ሲያይ፣ አንድም ቀን ቀና ብሎ የማለዳ ፀሐይ ጮራዋን ስትፈነጥቅ ወይም የወዳጆቹን ፈገግታ ሆነ የአበቦችን ፍካታ ሳያይ ኖረ። መሬት መሬት እያዩ መጓዝ ኪሳራው የከፋ ነው። ምድር ላይ መኖር የራሱ ግዴታ ቢኖርበትም፣ ከምድር ጋር እንዲህ መቆራኘት፣ ማንነትን እና አቅጣጫን ማሳቱ አይቀርም።  

Read 827677 times Last modified on Thursday, 17 November 2011 17:19

115380 comments

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.