×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:18

ሌላው መንገድ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ግምገማ ድርሰት

ሌላው መንገድ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎቻችን ከተለምዶ ውጭ የሕይወት ታሪካቸውን በመጽሐፍ አሳትመው እያሠራጩ ነው። ይህ አዲስ ክስተት ነው፤ የሚደገፍ ነው። ማን እንደሆኑ፣ ምን እንደሠሩ አስረግጠን ሳናውቅና በሠሩት ሥራ ዙሪያ ሳንወያይ ያለፉ የሕዝብ መሪዎች ጥቂቶች አይደሉምና ተዘርፈናል፣ ቅርስ ባክኖብናል። የአገራችንን ታሪካዊ ወቅቶች በግለሰቦቹ እይታ አስታከን ማገናዘብ ብሔራዊ መብታችን ብቻ ሳይሆን፣ የተመሠረተውን በጎ ከመርሳት የተነሳ ስሕተቶች እንዳይደገሙ፣ ፍርሃትና አሉባልታ እንዳይገዙን ለመከላከል ጭምር ይጠቅማል። በዚህ አጋጣሚ የጄኔራል ታዬ ጥላሁን የሕይወት ታሪክ እስካሁን አለመጻፉ ያሳስበናል። በዚሁ ድረ ገጽ፣ ከእስር ተፈተው ወደ ክርስቶስ አማንያን ማሕበር ተቀላቅያለሁ ያሉት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ፣ አሁን የእውነትን መንገድ ለይተው አውቀዋልና ሁሉን ግልጽ አድርገው በመጽሐፍ እንዲያሠፍሩ ማሳሰባችን ይታወሳል። ሌሎች፣ በተለይ ሴቶች ካሉ እንደዚሁ።

የዛሬው ትኩረታችን፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ባለፈው ወር፣ “ዳንዲ - የነጋሶ መንገድ” በሚል ርእስ ባሳተሙት መጽሐፍ ላይ ስለ ሰማእቱ ቄስ ጉዲና ቱምሳ ባሠፈሩት ላይ ብቻ ይሆናል። በነገራችን ላይ፣ ዶክተር ነጋሶ በቤተክርስቲያን አካባቢ የሚታወሱት በምዕራቡና በደቡብ-ምዕራቡ የአገራችን ክፍል የወንጌል አገልጋይና መሪ የነበሩት የቄስ ጊዳዳ ሶለን [በ1969 ዓ.ም. በ 78 ዓመታቸው ሞቱ] ልጅ በመሆናቸው ነው። ዶክተሩ፣ በመጽሐፋቸው ውስጥ ስለ ፍትሕ፣ በእግዚአብሔርና በሕግ ፊት ስለ ሰው ልጆች እኩልነት፣ ስለ ነፃነት ይገደኛል፤ ለዚህም ስታገል ኖሬአለሁ የማለታቸው መሠረቱ ምን እንደ ሆነ መገመት አያዳግትም። አባታቸው ቄስ ጊዳዳ [“ጊዳዳ” ትርጓሜው፦ “ለሕዝብ የሚያነባ” ማለት ሲሆን] በወንጌል ምክንያት የተሰደዱና ቤተክርስቲያን በመትከል የታወቁ የእምነት ሰው ነበሩ። በተጨማሪ፣ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት አሳድገው ለአገር መሪነት ያበቋቸውን እንደ እነ ክቡር አቶ አማኑኤል አብርሃምን፣ አቶ መርኪና መጃን፣ ኦነሲሞስ ነሲብን መጥቀስ ይቻላል። በአፍሪቃ የነፃነት ትግል ውስጥ ደግሞ ስመ-ጥር የሆኑት እነ ኔሬሬ፣ ማንዴላ፣ ካውንዳ፣ ንኵሩማ፣ ወዘተ፣ ከወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት የፈለቁ ናቸው። የቤተክርስቲያን አስተዋጽዖ እንደ ቀላል ሊታይ አይገባም ማለት ነው።

በ “ነጋሶ መንገድ” ላይ፦ ደርግ፣ቄስ ጉዲና ቱምሳንየገደለው፣ “የኦሮሞ ነፃነት ግንባር [ኦነግ] ናቸው ብሎሲሆንደርግከወደቀበኋላደግሞየቄሱአስከሬንከጅምላመቃብርወጥቶበስርዓትበተቀበረበትጊዜደርግቄሱንየገደለውየሃይማኖትነፃነትንለማፈንነበር ተብሎየተነገረውን ትክክል አይደለም ብለዋል። ለዚህም ማስረጃቸውን እንደሚከተለው አቅርበዋል፦ 1969 .ቄስጉዲናለቤተክርስቲያንስራወደጀርመንሲመጡእግረመንገዳቸውንከኦነግመልእክትይዘውመጥተውነበር።መልዕክቱንለመንገርመጀመሪያዲማነገዎማስትሬትዲግሪውንእያጠናከነበረበትሴኔጋልወደጀርመንእንዲመጣአደረጉናከዚያፍራንክፈርትከእኔጋርተገናኙ።ለእሱየመጣውመልዕክትጀርመንሀገርቢሮበመክፈትየኦነግወኪልሆኖእንዲሰራየሚልነበር።እኔደግሞዲማንእንድረዳነበርየተፈለገውሌላውቄስጉዲናየሰጡኝመረጃኦነግበመካከለኛውምስራቅአንድልዑክእንደሚልክናልዑኩበባሮቱምሳእንደሚመራየሚጠቁምነበር ቄስጉዲናንለመጨረሻጊዜያገኘኋቸውያኔነው።ደርግ፣ሀገርቤትሲገቡእስርቤትአስገብቶገደላቸውናከሌሎችጋርበጅምላተቀበሩ…” [ገጽ 110]።

ዶክተር ነጋሶ ማስረጃ ብለው ያቀረቡት አከራካሪ አይሆንም። ደርግ ቄስ ጉዲናን የገደለው ኦነግ ናቸው በሚል ሰበብ ነው። ይህን ስንል፣ ደርግ የወሰደው የግድያ እርምጃ ሆነ ያቀረበው ሰበብ ትክክል ነው ማለት አይደለም። ቄስ ጉዲናን በኦሮሞነታቸው ወይም በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ ፈርጆ ማለፍ ግን የኖሩለትንና የተሠውለትን የሕይወት ምስክርነት ማጕደፍ ይሆናል። ግለሰቡ ቁመተ-ረጂም፣ ከሠፈር ያለፈ ሰፊ አእምሮ የተለገሳቸው ነበሩና። ዶክተር ነጋሶ ይህን የሚክዱ አይመስለንም። በሌላ አነጋገር፣ የክርስቶስ ተከታይና የቤተክርስቲያኑ መሪ እንደሆኑ ከግምት ውስጥ ሳናስገባ ቄስ ጉዲናን ጠንቅቀን መረዳት አዳጋችና አሳሳች ይሆናል። ደርግ፣ ቄስ ጉዲናን የገደልኩት የቤተክርስቲያን መሪ በመሆናቸው ነው ሊል እንደማይችል ግልጽ ይመስለናል። በቤተክርስቲያን ላይ ስደት እና በአማንያን ላይ እስራት በታወጀበት ሰዓት የአምልኮ ነፃነት አለ አልልም ማለታቸው፤ ቀይና ነጭ ሽብር በየአውራ መንገዱ ያፈሰሰው ደም ሳይደርቅ እንዲህ የመሰለ አቋም መውሰድ ምን እንደሚያስከትል ለማንም ግልጽ ነው። በዚህ ላይ ወንድማቸው ባሮ ቱምሣ የአንጃ ፖለቲካ ፓርቲ መሪ ናቸው።

ቄስ ጉዲና የተሠውት በ 1971 ዓ.ም. በሃምሳ ዓመታቸው ነው። አመለካከታቸው ከጎሣና ከዘር ያለፈ ነው ስላልን መድገም አያሻንም። ጽሑፋቸውን ያነበበና ንግግራቸውን ያደመጠ ማንም እንደሚያውቀው ወንጌልን ከማሕበራዊ ፍትኅ ጋር አገናዝበው ማየት የተቻላቸው ግለሰብ ነበሩ። የክርስቶስን ወንጌል በቤተክርስቲያን ክልል መወሰን ወይም በማሕበረ ሰብ ጠርዝ ላይ መትከል፣ የወንጌልን “ብርሃን እና ጨው” ነት አለማጤን እንደሆነ የተረዱ መሪ ነበሩ። ለመንግሥት ሥጋት የሆኑት ከዚህ አመለካከታቸው የተነሳ ነው። ስለ ሰው ማንነት ያላቸው መረዳት ከወንጌል አስተምርሆ የመነጨ እንጂ ከሰብዓዊነት አመለካከት ብቻ የፈለቀ አልነበረም። ወንጌል፣ ሰው በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠሩን፣ ከዚህ የተነሳ ክቡር መሆኑን፣ በአዳማዊ ኃጢአት ምክንያት ከፈጣሪው፣ ከራሱ፣ ከባልጀራውና ከፍጥረት ሁሉ ጋር መቆራረጡን ያስተምራል። ይህም ከማርክሳዊ አመለካከት፣ ብርሃን ከጨለማ እንደሚለይ ይለያል። ወንጌል፦ ሰው ቁስ ብቻ ሳይሆን፣ ነፍስም መንፈስም ነው፤ በሥጋ በተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በኩል ከአምላኩ፣ ከራሱና ከሌላው ጋር የሚታረቅበት መንገድ ተዘጋጅቶለታል ይላል። እንግዲህ፣ እግዚአብሔርን ያላማከለ አመለካከት ሰውን ከኢኮኖሚያዊና ከማሕበራዊ ግንኙነቶቹ ነጥሎ ማየት እንደሚሳነው በደርግና አሁን በሚገዛው መንግሥታት የታየው አመራር በቂ ማስረጃ የሚሆን ይመስለናል።

ቄስ ጉዲና በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶች ማንበብና መጻፍ እንዲስፋፋ ከወጠኑትና ጥረት ካደረጉት መካከክል የመጀመሪያው ናቸው። አብዮት ከመፈንዳቱ በፊት፣ ማሕበራዊ ነውጥ ተቃርቧል፣ ቤተክርስቲያን መዘጋጀት አለባት ሲሉ እንደ ነበረ የሰሙ ዛሬም በሕይወት አሉ። ደርግ ሥልጣን ሲይዝ፣ ጸረ-ሃይማኖት/ጸረ-ክርስቲያን መመሪያ እንደሚያውጅ፣ ለዚህም ሥርዓት መበገር እንደማይገባ ጠንቅቀው ተረድተው ነበር። ንጉሥ ቢሆን፣ የፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር፣ የክርስቶስን ጌትነት ለሚቀናቀን ለማናቸውም ምድራዊ ሥልጣን ማጎንበስ አይገባም ይሉ ነበር።

ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው በምድር በሰማይ

እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዶክተር ነጋሶ ስለ ቄስ ጉዲና የነገሩን አዲስ ነገር የለም። ቄስ ጉዲና ኦሮሞ መሆናቸው፣ የመጣው ለውጥ ከአብራኩ ለወጡት ሕዝብ ያስገኘው ጥቅም አንሶ እያዩ ዝም አለማለታቸው እንደ ድንቅ ሊታይ አይገባም።  ዶክተር ነጋሶም እኮ ኦሮሞ ናቸው። ኦሮሞ ስለሆኑ፣ የሚታገሉት ለኦሮሞ ሕዝብ ብቻ ነው ማለት ታዲያ የትግላቸውን ፈር ባጭር አያስቀርም? ያስቀራል እንጂ። አያስቀርም ብንል፣ በመጽሐፋቸው ላይ እንደ ተመለከተው ለዲሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነትና ለሰብአዊ መብት መከበር ያደረጉት አስተዋጽዖ ያግደናል። ስለ ቄስ ጉዲና ግን ሊዘነጋ የማይገባ ጉዳይ፣ ደርግ በፍትኅ ስም የሚያካሄደውን ግድያና በደል አይተው ዝም አለማለታቸውና አለመተባበራቸው ነው። እኚህን ሰው በአንድ አንጃ መከለል አግባብ አይሆንም የምንለው ለዚህ ነው። የሰውን ሞላ ነፃ የሚያወጣውን የክርስቶስን ፍትሓዊ ወንጌል አቋማቸው ቢያደርጉ ድንቅ አይደለም ማለት ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዶክተር ነጋሶ፣ ኦነግ ናቸው ብለው ያቀረቡት ማስረጃ፣ ቄስ ጉዲና የክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪ ከመሆናቸውና ዘርና ጎሣ ከማይወስነው ፍትኀዊ ወንጌል አራማጅነታቸው አንዳች እንደማይቀንስ ነው። ባጭሩ፣ የጉዲናን ስነመለኮታዊና ማሕበራዊ አቋም መነጣጠል ሐቅን ማዛባትና የሌለ ስም መስጠት ይሆናል። 

መንግሥታት ሁሉ የሚቀናቀናቸውን ለማስወገድ የሚጠቀሙበት ዘዴ ተመሳሳይ ነው። የአሜሪካ መንግሥት፣ እ.አ.አ በ1968 ዓ.ም. የሰብአዊ መብት ተሟጋች የነበረውን ቄስ ማርቲን ሉተር ኪንግን [በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] የገደለው ኮሚዩኒስት ብሎ ነው። ማርቲን ኪንግ የአገሩን ዘረኛ ፖሊሲ መቃወሙ ብዙ ችግር አስከትሎበታል፤ የራሱና የቤተሰቡ ሕይወት እለት እለት ለአደጋ የተጋለጠ ነበር። የፍጻሜ እርምጃ የተወሰደበት ግን ከቤተክርስቲያን ክልል ወጣ ብሎ፣ አሜሪካ በቪዬትናም ስለምታካሄደው ሕገ ወጥ ጦርነት እና፣ በተለይም በኢኮኖሚ ረገድ በጥቁሮች ላይ የሚካሄደውን አድልዎና ግፍ መቃወምና ወደ ሰሜኑ የአሜሪካ ግዛት ዘልቆ ማደራጀት በጀመረበት ወቅት ነበር። ወንጌል ሙሉ የሚሆነው፣ ቤተክርስቲያን ነፍሳትን ወደ ክርስቶስ መንግሥት ከማምጣት ጋር ለማሕበራዊ ፍትኅ ስትታገል ጭምር ነው። ይህም ከፍተኛ መስዋእት ይጠይቃል፤ ፍሬው ደግሞ በደም ይደረጃል።

የጀርመን መንግሥት ቄስ ዲትሪኽ ቦንኦፈር [እ.አ.አ. በ1945 ዓ.ም. በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] እውነተኛዪቱ ቤተክርስቲያን፣ ይሁዲና ጂፕሲዎች እየታደኑ ባለበት ሰዓት፣ ማሕበረ ምእመኑን እንዳያስተምር አሳቡን በጽሑፍ እንዳያሠፍር በማገዱ ሂትለርን ለማስወገድ ከተደራጁት ጋር ለማበር ተገደደ። ያኔ ለቦንኦፈር ጥያቄ የሆነበትና ዛሬም ለኛ ጥያቄ ሊሆን የሚገባው፣ እንዴት ከተመረዘ ማሕበራዊ ሥርዓት ውስጥ ራስን ማዳን ይቻላል የሚለው ሳይሆን፣ የሚቀጥለው ትውልድ እንዴት ይሆናል? እንዴትስ ይኖራል? የሚለው ነው። ቦንኦፈር አሜሪካ ሄዶ በዚያው መቅረትና ተደላድሎ መኖር ሲችል፣ የሚያውቁት ሁሉ ‘አትሂድ፣ ችግሩ ይለፍ’ ሲሉት እምቢ ብሎ ወደ ትውልድ ምድሩ ወደ ጀርመን አገር የተመለሰው ሊገደል እንደሚችል ሳይጠረጥር ቀርቶ አይደለም።

የኢጣልያ ፋሺስት አቡነ ጴጥሮስን [በ 1928 ዓ.ም. በ 54 ዓመታቸው ተሠው] ገና አገራችንን እንደ ወረረ ወዲያው ያስገደለው አላስቀምጥ አላስተኛ ስላሉ ነው፤ ሕዝቡን ለአረመኔ ወራሪ አልገዝትም፣ የተቀበልኩትን የወንጌል አደራና ሕዝቡን አሳልፌ ከምሰጥ ብሠዋ ይሻለኛል ስላሉ ነው። ለሕይወታቸው አልሳሱም።

ቄስ ጉዲና፣ ቄስ ማርቲን፣ ቄስ ቦንኦፈር እና አቡነ ጴጥሮስ በተገኙበት ሰማእታት ናቸው። ሁሉም የወጡት ከክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው። የሞቱት በወንጌል ዓላማ ለፍትኅ ነው። በመጨረሻዋ ሰዓት የተናገሩትን ቃል ማገናዘብ ደግሞ የሕይወታቸውን ጥሪና ቁምነገር ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። ሰው ወደ ሞት ሲቃረብ የሚናገረው ከሌላው ጊዜ ይልቅ ተኣማኒነት ይኖረዋልና። ለዚህም ነው ወደ ሞት ለተቃረበ ሰው፦ ምን የምትለው ነገር አለህ? ተብሎ የመጨረሻ እድል የሚሰጠው።

ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ፣ በፋሺስት ገዳዮች ፊት ቆመው፦ “ሥጋንም የሚገድሉትን፣ ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ …” እያሉና ሕዝቡ እጁን እንዳይሰጥ እየመከሩ በጥይት ተደብድበው ሞቱ። ይህም፣ “ለጊዜው፣ በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ” የሚለውን ሐዋሪያዊ ቃል ያስታውሰናል [ማቴዎስ 10:28 እና ወደ ዕብራውያን 11:25]።

ማርቲንኪንግ የተጋበዘበት የምሽት ፕሮግራም ከመድረሱ በፊት፣ ሙዚቃ እንዲጫወት ለተመደበው ሰው፣ “ውድ ጌታ [ኢየሱስ] …እጄን ያዘኝ” የምትለዋን ዝማሬ ጥሩ አድርጎ እንዲጫወታት ደጋግሞ ጠይቆት ነበር። ቦንኦፈር ደግሞ፣ “እነሆ ፍጻሜው ደረሰ፣ ለኔ ግን የሕይወት ጅማሬ ነው” ብሎ ተንበርክኮ ከጸለየ በኋላ ተሰቀለ።

ለቄስ ጉዲና፣ “… እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ” የሚለው ቃል መመሪያቸው እንደነበር ተዘግቧል [2ኛ ቆሮንቶስ 5:15]። ተይዘው በተገደሉበት ምሽት፣ በኡራዔል መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ኢየሱስን ከሰበኩ በኋላ ኢየሱስን እያሰቡ ደጅ ወጡ። በጨለማ ተገን አፍነው ገደሏቸው። ነፍሳቸው ግን ወደ ዘላለሙ ብርሃን፣ የዓለም ብርሃን ወደ ሆነው ወደ ኢየሱስ አገር አመለጠች። ሃሌ ሉያ!

ታዲያ፣ አንድን ግለሰብ ሰማእት ነው የሚያሰኘው ምንድነው? ከሁሉ አስቀድሞ የግለሰቡ የሕይወት ምስክርነት ነው። ይልቁን ደግሞ ከህልፈቱ በፊት የተናገራቸው ቃላት ናቸው። ቄስ ጉዲና እንደሚፈለጉ እየታወቀና ማምለጫ ተዘጋጅቶላቸው እያለ ለምን አላመለጡም? ታስረው መፈታታቸው ማስጠንቀቂያ ሳይሆናቸው ቀርቶ ነው? ምሥጢሩ፣ ራሳቸውን የቤተክርስቲያኑ እረኛ ከሆነው ከኢየሱስ በታች የመንጋው እረኛ መሆናቸውን ጠንቅቀው የተረዱ ሰው ስለነበረ ነው። በታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ አማላጅነት ከእስር ተፈትተው፣ ከአገር እንዲወጡ አሳብ ሲቀርብላቸው፦ “እኔ የቤተክርስቲያን መሪ ሆኜ ሳለ፣ እንዴት በፈተና ሰዓት መንጋውን ትቼ እሸሻለሁ? ደግሞስ፣ ካህናቱን የትም አትሂዱ ብዬ እየተማፀንኳቸው ልሸሽ? አልሸሽም፣ አላደርገውም” ብለው ነበር የመለሱት። “መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል፣ በጎቹም ይበተናሉ” [ዮሐንስ 10:12]።

የ”ነጋሶ መንገድ” ይህን ዋነኛ ስነ መለኮታዊ መረዳት የዘነጋው ይመስላል። ምናልባት መጽሐፉ የተጻፈው ከዚህ አኳያ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል። ወቅቱ በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ላይ መንግሥት የስደት እና የእሥራት ዘመቻ የሚያካሄድበት ሰዓት ነበር። ቄስ ጉዲና የሚመሩት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ደግሞ ብዙ እንቅስቃሴዋ በውጭው ዓለም እና በምዕራብና ደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ መሆኑ፣ የኦነግ መሪዎችም [ዶክተር ነጋሶን ጨምሮ] አብዛኛዎቹ ከቤተክርስቲያንና ከዚሁ ክፍለ ሃገር የወጡ መሆናቸው ለመንግሥት ሥጋት ፈጥሮ ነበር። ከዚህ የተነሳ ቤተክርስቲያንና መሪዎቿን በዐይነ ቁራኛ መከታተል ግድ ሆነ፤ አድራጎቱም፣ የመንግሥትን ኢፍትኀዊ አመራር አደባባይ አወጣው።

ከዚህ መጽሐፍ ጋር በተያያዘ አንድ የሚከነክነንን ጉዳይ እናንሳና እንጨርስ። ለመሆኑ፣ የአገራችን ምሑራን ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ዘላቂ የሆነ ምን ማሕበራዊ አስተዋጽኦ ወይም መፍትሔ አስገኝተዋል? በመደብና በጎሣ ሕዝቡን ከፋፍለው አለመተማመንን ዘርተውበታል፤ ይህን አይተናል። ያውቃሉ የተባሉት እርስ በርስ መስማማት ሆነ መከባበር ተስኖአቸዋል። አገሪቷን ወዴት መምራት እንደሚገባቸው ገና እርግጠኞች አይደሉም፤ የሌሎችን አሳብ ለመስማት አይፈቀዱም። የጋራ በሆነች አገር፣ ያልተስማማቸውን የማግለልና የማውገዝ ባሕል ተጠናውቶአቸዋል። ይህንና ያን ሲሉ ስንት ትውልድ ፈጁ፤ በሙከራ ብቻ ምድሪቷን አስረጁ። ቤተክርስቲያንን ከሚያፈርስ፣ ፈርሃ እግዚአብሔርን ከሚሸረሽር አድራጎት ሊቆጠቡ አልቻሉም። ቤተክርስቲያንን ለዓላማቸው ከመጠቀም አልቦዘኑም። የክርስቶስን ወንጌል ከባህል፣ ከአፈ-ታሪክና ከጎሠኛ አስተሳሰብ ለይተው ስለማያዩ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑን ያምሳሉ። “እግዚአብሔር የለም” ያሉንና ሊያሰኙን ያንገላቱን ዛሬ ወዴት አሉ? የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ግን ዛሬም አለች፣ ጌታዋ ሕያው ስለሆነ፣ ሕያው ነች። እግዚአብሔርን የማይፈሩ፣ እግዚአብሔር የማያይ የመሰላቸው ሕዝብን ሲበድሉና ሲያንገላቱ፣ ለወገኔ ይጠቅማል ማለት ሲያበዙ፣ የምሕረት እጁን ስለ ዘረጋ እንጂ፣ ዝምታው ስለማይፈርድ አለመሆኑን አላስተዋሉም። እግዚአብሔር ሳ-ይ-ፈ-ራ ሕዝብ አይዋደድም፤ እግዚአብሔር ሳይከበር ሕዝብ አይከበርም፤ አይከባበርም።

“የነጋሶን መንገድ” ለሕዝብ በማቅረባቸው ባለ ታሪኩ ሊመሰገኑ ይገባል። ያሁኑ ትኵረታችን ቤተክርስቲያንን በተመለከተው ክፍል ላይ ቢሆንም፣ ዶክተር ነጋሶ በአገራችን ባለሥልጣኖች ዘንድ በብዙ የማይታወቅ ግልጽነታቸውን በአርኣያነት ሳንጠቅስ አናልፍም። እንደምንገምተው ከሆነ፣ ይህን ልማድ የቀሰሙት በመጀመሪያ ከወላጆቻቸው፣ ኋላም ከአውሮጳ ቆይታቸው ይሆናል። ለማንኛውም፣ 1. የአገር መሪ በሕይወት እያለ ከሥልጣን ወርዶ በሕዝብ መካከል እንደ ተራ ዜጋ መኖር፤ 2. የአገራችን ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በተጠየቁ እለት እንደ ፈሩና ሌላ ሰው ፈልጉ እንዳሉ መግለጻቸው፤ 3. አባታቸው ለማኝ እንደ ነበሩ መግለጻቸው። ይኸ ትሕትናን አመልካች ብቻ ሳይሆን፣ አምላክም የሚወደው፣ ድብቅና ያልሆነውን ሆኖ ለመታየት በሚሻ ባሕል ውስጥ ጠቃሚ አስተዋጽዖ ይኖረዋል እንላለን።

እንግዲህ፣ “የነጋሶ መንገድ” እነሆ። ሌላው መንገድ የክርስቶስ እና የተከታዮቹ መንገድ ነው። የአገራችን ምሑሩ ክፍል ሃምሳ ዓመት የተጓዘበት መንገድ የእግዚአብሔር ፍርሃት የሌለበት ምድረ በዳ ነበረ፤ አላዋጣም። የእረፍት እህል፣ የእረፍት ውሃና ሰላም አላመጣም። አለማዋጣቱ በሥጋና በነፍሱ ላይ ጠባሳ ትቶ አልፏል። ደርግና ምሑራኑ እግዚአብሔርን ሻሩ፤ በመጤ ፍልስፍና የመደብ ልዩነት ብለው ምድሪቷን አመሳቀሉ። ደርግን ተቃውመው የተነሱ ተራ ሲደርሳቸው በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን ሰው በጎሣ ልዩነት አቃቃሩ። ሁለቱም የእግዚአብሔርን ፍርሃት አጥብቀው ተጻረሩ። ኧረ ለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መሪዎችና ምሑራን የሚማሩት መቼ ይሆን? ለ “ክርስቶስ መንገድ” የሚለቁለትስ መቼ ይሆን?! 

Read 10707930 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 22:03

1549632 comments

  • Comment Link question Wednesday, 28 January 2026 12:39 posted by question

    I’ve been checking out Paybis for a while
    now, especially after ending up broke, and I’m still not completely certain whether it deserves all the attention it gets.
    Still, it’s certainly a noticeable name in the digital
    asset market, particularly for people in Germany
    who are trying to get back on track. From what I understand, Paybis presents itself as a large-scale cryptocurrency
    service that supports standard payment methods, something many platforms either
    limit or complicate.

    What initially caught my eye is how Paybis seems to connect traditional
    German banking methods with the crypto world. Many exchanges focus only on crypto-to-crypto trades, while Paybis allows users
    to buy crypto using debit cards. I’m not saying the process is perfect, but it does
    seem aimed at people starting out rather than just advanced traders.



    Another aspect worth noting is the selection of
    supported assets. Paybis doesn’t restrict itself to Bitcoin and Ethereum only.
    Instead, it offers a wider range of digital assets, which might attract users who are diversifying.

    Still, things like liquidity are worth checking before making decisions.


    Security and compliance also come up often around Paybis.
    The platform highlights identity verification, which can feel professional for users in Germany, though others might see it as restrictive.
    I’m still undecided, but it does suggest Paybis tries to operate as a regulated marketplace.



    When it comes to fees, reviews seem divided.
    Some say Paybis is clear about costs, while others note that pricing can vary by payment method.
    This isn’t unusual in the crypto industry, but it means users should
    research properly before moving money.

    Overall, I wouldn’t call Paybis the best option, but
    it does seem like a platform worth checking out, especially for someone in Germany trying to build a new starting point.
    I’m still forming my opinion, but it seems interesting enough to justify further research.

  • Comment Link pinup_gjEl Wednesday, 28 January 2026 12:37 posted by pinup_gjEl

    pin up crash game pinup2003.help

  • Comment Link asansör servisi Wednesday, 28 January 2026 12:34 posted by asansör servisi

    Havee you ever thought about adding a little bit more
    than just your articles? I mean, wht you say is fundamental annd everything.
    Nevertheless think of if yoou added some great pictures or videos
    to give your posts more, "pop"! Your content is excellent but with pics and videos, this ebsite could
    cergainly be one of thhe most beneficial iin its niche.
    Fantastic blog!

  • Comment Link Hiltonsnade Wednesday, 28 January 2026 12:34 posted by Hiltonsnade

    ремонт стекла айфона замена sim коннектора iphone

  • Comment Link GeorgeGauri Wednesday, 28 January 2026 12:34 posted by GeorgeGauri

    Монтаж снегозадержателей на фальцевую кровлю. Устанавливаем специальные кронштейны, которые не нарушают целостность покрытия. Безопасный и контролируемый сход снега, защита водостоков и людей ниже. Необходимый элемент для металлических крыш. krovlyamolodechno.ru

  • Comment Link Jackso Wednesday, 28 January 2026 12:30 posted by Jackso

    https://williamg2.livejournal.com/713.html?newpost=1

  • Comment Link Reiki Master Certification Wednesday, 28 January 2026 12:27 posted by Reiki Master Certification

    trumpkennedycenter.org has Patreon Leaked Content and it's easy, cheap and fake

  • Comment Link SpeedAU Wednesday, 28 January 2026 12:25 posted by SpeedAU

    This piece of writing will help the internet users for creating
    new web site or even a blog from start to
    end.

  • Comment Link 일회용 전자담배 Wednesday, 28 January 2026 12:24 posted by 일회용 전자담배

    Wow, that's what I was searching for, what a material!
    existing here at this website, thanks admin of this website.

  • Comment Link Diploma Maker Service Wednesday, 28 January 2026 12:24 posted by Diploma Maker Service

    trumpkennedycenter.com has Black Widow Spider and it's easy, cheap and fake

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.