×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:18

ሌላው መንገድ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ግምገማ ድርሰት

ሌላው መንገድ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎቻችን ከተለምዶ ውጭ የሕይወት ታሪካቸውን በመጽሐፍ አሳትመው እያሠራጩ ነው። ይህ አዲስ ክስተት ነው፤ የሚደገፍ ነው። ማን እንደሆኑ፣ ምን እንደሠሩ አስረግጠን ሳናውቅና በሠሩት ሥራ ዙሪያ ሳንወያይ ያለፉ የሕዝብ መሪዎች ጥቂቶች አይደሉምና ተዘርፈናል፣ ቅርስ ባክኖብናል። የአገራችንን ታሪካዊ ወቅቶች በግለሰቦቹ እይታ አስታከን ማገናዘብ ብሔራዊ መብታችን ብቻ ሳይሆን፣ የተመሠረተውን በጎ ከመርሳት የተነሳ ስሕተቶች እንዳይደገሙ፣ ፍርሃትና አሉባልታ እንዳይገዙን ለመከላከል ጭምር ይጠቅማል። በዚህ አጋጣሚ የጄኔራል ታዬ ጥላሁን የሕይወት ታሪክ እስካሁን አለመጻፉ ያሳስበናል። በዚሁ ድረ ገጽ፣ ከእስር ተፈተው ወደ ክርስቶስ አማንያን ማሕበር ተቀላቅያለሁ ያሉት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ፣ አሁን የእውነትን መንገድ ለይተው አውቀዋልና ሁሉን ግልጽ አድርገው በመጽሐፍ እንዲያሠፍሩ ማሳሰባችን ይታወሳል። ሌሎች፣ በተለይ ሴቶች ካሉ እንደዚሁ።

የዛሬው ትኩረታችን፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ባለፈው ወር፣ “ዳንዲ - የነጋሶ መንገድ” በሚል ርእስ ባሳተሙት መጽሐፍ ላይ ስለ ሰማእቱ ቄስ ጉዲና ቱምሳ ባሠፈሩት ላይ ብቻ ይሆናል። በነገራችን ላይ፣ ዶክተር ነጋሶ በቤተክርስቲያን አካባቢ የሚታወሱት በምዕራቡና በደቡብ-ምዕራቡ የአገራችን ክፍል የወንጌል አገልጋይና መሪ የነበሩት የቄስ ጊዳዳ ሶለን [በ1969 ዓ.ም. በ 78 ዓመታቸው ሞቱ] ልጅ በመሆናቸው ነው። ዶክተሩ፣ በመጽሐፋቸው ውስጥ ስለ ፍትሕ፣ በእግዚአብሔርና በሕግ ፊት ስለ ሰው ልጆች እኩልነት፣ ስለ ነፃነት ይገደኛል፤ ለዚህም ስታገል ኖሬአለሁ የማለታቸው መሠረቱ ምን እንደ ሆነ መገመት አያዳግትም። አባታቸው ቄስ ጊዳዳ [“ጊዳዳ” ትርጓሜው፦ “ለሕዝብ የሚያነባ” ማለት ሲሆን] በወንጌል ምክንያት የተሰደዱና ቤተክርስቲያን በመትከል የታወቁ የእምነት ሰው ነበሩ። በተጨማሪ፣ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት አሳድገው ለአገር መሪነት ያበቋቸውን እንደ እነ ክቡር አቶ አማኑኤል አብርሃምን፣ አቶ መርኪና መጃን፣ ኦነሲሞስ ነሲብን መጥቀስ ይቻላል። በአፍሪቃ የነፃነት ትግል ውስጥ ደግሞ ስመ-ጥር የሆኑት እነ ኔሬሬ፣ ማንዴላ፣ ካውንዳ፣ ንኵሩማ፣ ወዘተ፣ ከወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት የፈለቁ ናቸው። የቤተክርስቲያን አስተዋጽዖ እንደ ቀላል ሊታይ አይገባም ማለት ነው።

በ “ነጋሶ መንገድ” ላይ፦ ደርግ፣ቄስ ጉዲና ቱምሳንየገደለው፣ “የኦሮሞ ነፃነት ግንባር [ኦነግ] ናቸው ብሎሲሆንደርግከወደቀበኋላደግሞየቄሱአስከሬንከጅምላመቃብርወጥቶበስርዓትበተቀበረበትጊዜደርግቄሱንየገደለውየሃይማኖትነፃነትንለማፈንነበር ተብሎየተነገረውን ትክክል አይደለም ብለዋል። ለዚህም ማስረጃቸውን እንደሚከተለው አቅርበዋል፦ 1969 .ቄስጉዲናለቤተክርስቲያንስራወደጀርመንሲመጡእግረመንገዳቸውንከኦነግመልእክትይዘውመጥተውነበር።መልዕክቱንለመንገርመጀመሪያዲማነገዎማስትሬትዲግሪውንእያጠናከነበረበትሴኔጋልወደጀርመንእንዲመጣአደረጉናከዚያፍራንክፈርትከእኔጋርተገናኙ።ለእሱየመጣውመልዕክትጀርመንሀገርቢሮበመክፈትየኦነግወኪልሆኖእንዲሰራየሚልነበር።እኔደግሞዲማንእንድረዳነበርየተፈለገውሌላውቄስጉዲናየሰጡኝመረጃኦነግበመካከለኛውምስራቅአንድልዑክእንደሚልክናልዑኩበባሮቱምሳእንደሚመራየሚጠቁምነበር ቄስጉዲናንለመጨረሻጊዜያገኘኋቸውያኔነው።ደርግ፣ሀገርቤትሲገቡእስርቤትአስገብቶገደላቸውናከሌሎችጋርበጅምላተቀበሩ…” [ገጽ 110]።

ዶክተር ነጋሶ ማስረጃ ብለው ያቀረቡት አከራካሪ አይሆንም። ደርግ ቄስ ጉዲናን የገደለው ኦነግ ናቸው በሚል ሰበብ ነው። ይህን ስንል፣ ደርግ የወሰደው የግድያ እርምጃ ሆነ ያቀረበው ሰበብ ትክክል ነው ማለት አይደለም። ቄስ ጉዲናን በኦሮሞነታቸው ወይም በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ ፈርጆ ማለፍ ግን የኖሩለትንና የተሠውለትን የሕይወት ምስክርነት ማጕደፍ ይሆናል። ግለሰቡ ቁመተ-ረጂም፣ ከሠፈር ያለፈ ሰፊ አእምሮ የተለገሳቸው ነበሩና። ዶክተር ነጋሶ ይህን የሚክዱ አይመስለንም። በሌላ አነጋገር፣ የክርስቶስ ተከታይና የቤተክርስቲያኑ መሪ እንደሆኑ ከግምት ውስጥ ሳናስገባ ቄስ ጉዲናን ጠንቅቀን መረዳት አዳጋችና አሳሳች ይሆናል። ደርግ፣ ቄስ ጉዲናን የገደልኩት የቤተክርስቲያን መሪ በመሆናቸው ነው ሊል እንደማይችል ግልጽ ይመስለናል። በቤተክርስቲያን ላይ ስደት እና በአማንያን ላይ እስራት በታወጀበት ሰዓት የአምልኮ ነፃነት አለ አልልም ማለታቸው፤ ቀይና ነጭ ሽብር በየአውራ መንገዱ ያፈሰሰው ደም ሳይደርቅ እንዲህ የመሰለ አቋም መውሰድ ምን እንደሚያስከትል ለማንም ግልጽ ነው። በዚህ ላይ ወንድማቸው ባሮ ቱምሣ የአንጃ ፖለቲካ ፓርቲ መሪ ናቸው።

ቄስ ጉዲና የተሠውት በ 1971 ዓ.ም. በሃምሳ ዓመታቸው ነው። አመለካከታቸው ከጎሣና ከዘር ያለፈ ነው ስላልን መድገም አያሻንም። ጽሑፋቸውን ያነበበና ንግግራቸውን ያደመጠ ማንም እንደሚያውቀው ወንጌልን ከማሕበራዊ ፍትኅ ጋር አገናዝበው ማየት የተቻላቸው ግለሰብ ነበሩ። የክርስቶስን ወንጌል በቤተክርስቲያን ክልል መወሰን ወይም በማሕበረ ሰብ ጠርዝ ላይ መትከል፣ የወንጌልን “ብርሃን እና ጨው” ነት አለማጤን እንደሆነ የተረዱ መሪ ነበሩ። ለመንግሥት ሥጋት የሆኑት ከዚህ አመለካከታቸው የተነሳ ነው። ስለ ሰው ማንነት ያላቸው መረዳት ከወንጌል አስተምርሆ የመነጨ እንጂ ከሰብዓዊነት አመለካከት ብቻ የፈለቀ አልነበረም። ወንጌል፣ ሰው በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠሩን፣ ከዚህ የተነሳ ክቡር መሆኑን፣ በአዳማዊ ኃጢአት ምክንያት ከፈጣሪው፣ ከራሱ፣ ከባልጀራውና ከፍጥረት ሁሉ ጋር መቆራረጡን ያስተምራል። ይህም ከማርክሳዊ አመለካከት፣ ብርሃን ከጨለማ እንደሚለይ ይለያል። ወንጌል፦ ሰው ቁስ ብቻ ሳይሆን፣ ነፍስም መንፈስም ነው፤ በሥጋ በተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በኩል ከአምላኩ፣ ከራሱና ከሌላው ጋር የሚታረቅበት መንገድ ተዘጋጅቶለታል ይላል። እንግዲህ፣ እግዚአብሔርን ያላማከለ አመለካከት ሰውን ከኢኮኖሚያዊና ከማሕበራዊ ግንኙነቶቹ ነጥሎ ማየት እንደሚሳነው በደርግና አሁን በሚገዛው መንግሥታት የታየው አመራር በቂ ማስረጃ የሚሆን ይመስለናል።

ቄስ ጉዲና በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶች ማንበብና መጻፍ እንዲስፋፋ ከወጠኑትና ጥረት ካደረጉት መካከክል የመጀመሪያው ናቸው። አብዮት ከመፈንዳቱ በፊት፣ ማሕበራዊ ነውጥ ተቃርቧል፣ ቤተክርስቲያን መዘጋጀት አለባት ሲሉ እንደ ነበረ የሰሙ ዛሬም በሕይወት አሉ። ደርግ ሥልጣን ሲይዝ፣ ጸረ-ሃይማኖት/ጸረ-ክርስቲያን መመሪያ እንደሚያውጅ፣ ለዚህም ሥርዓት መበገር እንደማይገባ ጠንቅቀው ተረድተው ነበር። ንጉሥ ቢሆን፣ የፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር፣ የክርስቶስን ጌትነት ለሚቀናቀን ለማናቸውም ምድራዊ ሥልጣን ማጎንበስ አይገባም ይሉ ነበር።

ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው በምድር በሰማይ

እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዶክተር ነጋሶ ስለ ቄስ ጉዲና የነገሩን አዲስ ነገር የለም። ቄስ ጉዲና ኦሮሞ መሆናቸው፣ የመጣው ለውጥ ከአብራኩ ለወጡት ሕዝብ ያስገኘው ጥቅም አንሶ እያዩ ዝም አለማለታቸው እንደ ድንቅ ሊታይ አይገባም።  ዶክተር ነጋሶም እኮ ኦሮሞ ናቸው። ኦሮሞ ስለሆኑ፣ የሚታገሉት ለኦሮሞ ሕዝብ ብቻ ነው ማለት ታዲያ የትግላቸውን ፈር ባጭር አያስቀርም? ያስቀራል እንጂ። አያስቀርም ብንል፣ በመጽሐፋቸው ላይ እንደ ተመለከተው ለዲሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነትና ለሰብአዊ መብት መከበር ያደረጉት አስተዋጽዖ ያግደናል። ስለ ቄስ ጉዲና ግን ሊዘነጋ የማይገባ ጉዳይ፣ ደርግ በፍትኅ ስም የሚያካሄደውን ግድያና በደል አይተው ዝም አለማለታቸውና አለመተባበራቸው ነው። እኚህን ሰው በአንድ አንጃ መከለል አግባብ አይሆንም የምንለው ለዚህ ነው። የሰውን ሞላ ነፃ የሚያወጣውን የክርስቶስን ፍትሓዊ ወንጌል አቋማቸው ቢያደርጉ ድንቅ አይደለም ማለት ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዶክተር ነጋሶ፣ ኦነግ ናቸው ብለው ያቀረቡት ማስረጃ፣ ቄስ ጉዲና የክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪ ከመሆናቸውና ዘርና ጎሣ ከማይወስነው ፍትኀዊ ወንጌል አራማጅነታቸው አንዳች እንደማይቀንስ ነው። ባጭሩ፣ የጉዲናን ስነመለኮታዊና ማሕበራዊ አቋም መነጣጠል ሐቅን ማዛባትና የሌለ ስም መስጠት ይሆናል። 

መንግሥታት ሁሉ የሚቀናቀናቸውን ለማስወገድ የሚጠቀሙበት ዘዴ ተመሳሳይ ነው። የአሜሪካ መንግሥት፣ እ.አ.አ በ1968 ዓ.ም. የሰብአዊ መብት ተሟጋች የነበረውን ቄስ ማርቲን ሉተር ኪንግን [በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] የገደለው ኮሚዩኒስት ብሎ ነው። ማርቲን ኪንግ የአገሩን ዘረኛ ፖሊሲ መቃወሙ ብዙ ችግር አስከትሎበታል፤ የራሱና የቤተሰቡ ሕይወት እለት እለት ለአደጋ የተጋለጠ ነበር። የፍጻሜ እርምጃ የተወሰደበት ግን ከቤተክርስቲያን ክልል ወጣ ብሎ፣ አሜሪካ በቪዬትናም ስለምታካሄደው ሕገ ወጥ ጦርነት እና፣ በተለይም በኢኮኖሚ ረገድ በጥቁሮች ላይ የሚካሄደውን አድልዎና ግፍ መቃወምና ወደ ሰሜኑ የአሜሪካ ግዛት ዘልቆ ማደራጀት በጀመረበት ወቅት ነበር። ወንጌል ሙሉ የሚሆነው፣ ቤተክርስቲያን ነፍሳትን ወደ ክርስቶስ መንግሥት ከማምጣት ጋር ለማሕበራዊ ፍትኅ ስትታገል ጭምር ነው። ይህም ከፍተኛ መስዋእት ይጠይቃል፤ ፍሬው ደግሞ በደም ይደረጃል።

የጀርመን መንግሥት ቄስ ዲትሪኽ ቦንኦፈር [እ.አ.አ. በ1945 ዓ.ም. በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] እውነተኛዪቱ ቤተክርስቲያን፣ ይሁዲና ጂፕሲዎች እየታደኑ ባለበት ሰዓት፣ ማሕበረ ምእመኑን እንዳያስተምር አሳቡን በጽሑፍ እንዳያሠፍር በማገዱ ሂትለርን ለማስወገድ ከተደራጁት ጋር ለማበር ተገደደ። ያኔ ለቦንኦፈር ጥያቄ የሆነበትና ዛሬም ለኛ ጥያቄ ሊሆን የሚገባው፣ እንዴት ከተመረዘ ማሕበራዊ ሥርዓት ውስጥ ራስን ማዳን ይቻላል የሚለው ሳይሆን፣ የሚቀጥለው ትውልድ እንዴት ይሆናል? እንዴትስ ይኖራል? የሚለው ነው። ቦንኦፈር አሜሪካ ሄዶ በዚያው መቅረትና ተደላድሎ መኖር ሲችል፣ የሚያውቁት ሁሉ ‘አትሂድ፣ ችግሩ ይለፍ’ ሲሉት እምቢ ብሎ ወደ ትውልድ ምድሩ ወደ ጀርመን አገር የተመለሰው ሊገደል እንደሚችል ሳይጠረጥር ቀርቶ አይደለም።

የኢጣልያ ፋሺስት አቡነ ጴጥሮስን [በ 1928 ዓ.ም. በ 54 ዓመታቸው ተሠው] ገና አገራችንን እንደ ወረረ ወዲያው ያስገደለው አላስቀምጥ አላስተኛ ስላሉ ነው፤ ሕዝቡን ለአረመኔ ወራሪ አልገዝትም፣ የተቀበልኩትን የወንጌል አደራና ሕዝቡን አሳልፌ ከምሰጥ ብሠዋ ይሻለኛል ስላሉ ነው። ለሕይወታቸው አልሳሱም።

ቄስ ጉዲና፣ ቄስ ማርቲን፣ ቄስ ቦንኦፈር እና አቡነ ጴጥሮስ በተገኙበት ሰማእታት ናቸው። ሁሉም የወጡት ከክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው። የሞቱት በወንጌል ዓላማ ለፍትኅ ነው። በመጨረሻዋ ሰዓት የተናገሩትን ቃል ማገናዘብ ደግሞ የሕይወታቸውን ጥሪና ቁምነገር ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። ሰው ወደ ሞት ሲቃረብ የሚናገረው ከሌላው ጊዜ ይልቅ ተኣማኒነት ይኖረዋልና። ለዚህም ነው ወደ ሞት ለተቃረበ ሰው፦ ምን የምትለው ነገር አለህ? ተብሎ የመጨረሻ እድል የሚሰጠው።

ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ፣ በፋሺስት ገዳዮች ፊት ቆመው፦ “ሥጋንም የሚገድሉትን፣ ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ …” እያሉና ሕዝቡ እጁን እንዳይሰጥ እየመከሩ በጥይት ተደብድበው ሞቱ። ይህም፣ “ለጊዜው፣ በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ” የሚለውን ሐዋሪያዊ ቃል ያስታውሰናል [ማቴዎስ 10:28 እና ወደ ዕብራውያን 11:25]።

ማርቲንኪንግ የተጋበዘበት የምሽት ፕሮግራም ከመድረሱ በፊት፣ ሙዚቃ እንዲጫወት ለተመደበው ሰው፣ “ውድ ጌታ [ኢየሱስ] …እጄን ያዘኝ” የምትለዋን ዝማሬ ጥሩ አድርጎ እንዲጫወታት ደጋግሞ ጠይቆት ነበር። ቦንኦፈር ደግሞ፣ “እነሆ ፍጻሜው ደረሰ፣ ለኔ ግን የሕይወት ጅማሬ ነው” ብሎ ተንበርክኮ ከጸለየ በኋላ ተሰቀለ።

ለቄስ ጉዲና፣ “… እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ” የሚለው ቃል መመሪያቸው እንደነበር ተዘግቧል [2ኛ ቆሮንቶስ 5:15]። ተይዘው በተገደሉበት ምሽት፣ በኡራዔል መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ኢየሱስን ከሰበኩ በኋላ ኢየሱስን እያሰቡ ደጅ ወጡ። በጨለማ ተገን አፍነው ገደሏቸው። ነፍሳቸው ግን ወደ ዘላለሙ ብርሃን፣ የዓለም ብርሃን ወደ ሆነው ወደ ኢየሱስ አገር አመለጠች። ሃሌ ሉያ!

ታዲያ፣ አንድን ግለሰብ ሰማእት ነው የሚያሰኘው ምንድነው? ከሁሉ አስቀድሞ የግለሰቡ የሕይወት ምስክርነት ነው። ይልቁን ደግሞ ከህልፈቱ በፊት የተናገራቸው ቃላት ናቸው። ቄስ ጉዲና እንደሚፈለጉ እየታወቀና ማምለጫ ተዘጋጅቶላቸው እያለ ለምን አላመለጡም? ታስረው መፈታታቸው ማስጠንቀቂያ ሳይሆናቸው ቀርቶ ነው? ምሥጢሩ፣ ራሳቸውን የቤተክርስቲያኑ እረኛ ከሆነው ከኢየሱስ በታች የመንጋው እረኛ መሆናቸውን ጠንቅቀው የተረዱ ሰው ስለነበረ ነው። በታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ አማላጅነት ከእስር ተፈትተው፣ ከአገር እንዲወጡ አሳብ ሲቀርብላቸው፦ “እኔ የቤተክርስቲያን መሪ ሆኜ ሳለ፣ እንዴት በፈተና ሰዓት መንጋውን ትቼ እሸሻለሁ? ደግሞስ፣ ካህናቱን የትም አትሂዱ ብዬ እየተማፀንኳቸው ልሸሽ? አልሸሽም፣ አላደርገውም” ብለው ነበር የመለሱት። “መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል፣ በጎቹም ይበተናሉ” [ዮሐንስ 10:12]።

የ”ነጋሶ መንገድ” ይህን ዋነኛ ስነ መለኮታዊ መረዳት የዘነጋው ይመስላል። ምናልባት መጽሐፉ የተጻፈው ከዚህ አኳያ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል። ወቅቱ በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ላይ መንግሥት የስደት እና የእሥራት ዘመቻ የሚያካሄድበት ሰዓት ነበር። ቄስ ጉዲና የሚመሩት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ደግሞ ብዙ እንቅስቃሴዋ በውጭው ዓለም እና በምዕራብና ደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ መሆኑ፣ የኦነግ መሪዎችም [ዶክተር ነጋሶን ጨምሮ] አብዛኛዎቹ ከቤተክርስቲያንና ከዚሁ ክፍለ ሃገር የወጡ መሆናቸው ለመንግሥት ሥጋት ፈጥሮ ነበር። ከዚህ የተነሳ ቤተክርስቲያንና መሪዎቿን በዐይነ ቁራኛ መከታተል ግድ ሆነ፤ አድራጎቱም፣ የመንግሥትን ኢፍትኀዊ አመራር አደባባይ አወጣው።

ከዚህ መጽሐፍ ጋር በተያያዘ አንድ የሚከነክነንን ጉዳይ እናንሳና እንጨርስ። ለመሆኑ፣ የአገራችን ምሑራን ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ዘላቂ የሆነ ምን ማሕበራዊ አስተዋጽኦ ወይም መፍትሔ አስገኝተዋል? በመደብና በጎሣ ሕዝቡን ከፋፍለው አለመተማመንን ዘርተውበታል፤ ይህን አይተናል። ያውቃሉ የተባሉት እርስ በርስ መስማማት ሆነ መከባበር ተስኖአቸዋል። አገሪቷን ወዴት መምራት እንደሚገባቸው ገና እርግጠኞች አይደሉም፤ የሌሎችን አሳብ ለመስማት አይፈቀዱም። የጋራ በሆነች አገር፣ ያልተስማማቸውን የማግለልና የማውገዝ ባሕል ተጠናውቶአቸዋል። ይህንና ያን ሲሉ ስንት ትውልድ ፈጁ፤ በሙከራ ብቻ ምድሪቷን አስረጁ። ቤተክርስቲያንን ከሚያፈርስ፣ ፈርሃ እግዚአብሔርን ከሚሸረሽር አድራጎት ሊቆጠቡ አልቻሉም። ቤተክርስቲያንን ለዓላማቸው ከመጠቀም አልቦዘኑም። የክርስቶስን ወንጌል ከባህል፣ ከአፈ-ታሪክና ከጎሠኛ አስተሳሰብ ለይተው ስለማያዩ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑን ያምሳሉ። “እግዚአብሔር የለም” ያሉንና ሊያሰኙን ያንገላቱን ዛሬ ወዴት አሉ? የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ግን ዛሬም አለች፣ ጌታዋ ሕያው ስለሆነ፣ ሕያው ነች። እግዚአብሔርን የማይፈሩ፣ እግዚአብሔር የማያይ የመሰላቸው ሕዝብን ሲበድሉና ሲያንገላቱ፣ ለወገኔ ይጠቅማል ማለት ሲያበዙ፣ የምሕረት እጁን ስለ ዘረጋ እንጂ፣ ዝምታው ስለማይፈርድ አለመሆኑን አላስተዋሉም። እግዚአብሔር ሳ-ይ-ፈ-ራ ሕዝብ አይዋደድም፤ እግዚአብሔር ሳይከበር ሕዝብ አይከበርም፤ አይከባበርም።

“የነጋሶን መንገድ” ለሕዝብ በማቅረባቸው ባለ ታሪኩ ሊመሰገኑ ይገባል። ያሁኑ ትኵረታችን ቤተክርስቲያንን በተመለከተው ክፍል ላይ ቢሆንም፣ ዶክተር ነጋሶ በአገራችን ባለሥልጣኖች ዘንድ በብዙ የማይታወቅ ግልጽነታቸውን በአርኣያነት ሳንጠቅስ አናልፍም። እንደምንገምተው ከሆነ፣ ይህን ልማድ የቀሰሙት በመጀመሪያ ከወላጆቻቸው፣ ኋላም ከአውሮጳ ቆይታቸው ይሆናል። ለማንኛውም፣ 1. የአገር መሪ በሕይወት እያለ ከሥልጣን ወርዶ በሕዝብ መካከል እንደ ተራ ዜጋ መኖር፤ 2. የአገራችን ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በተጠየቁ እለት እንደ ፈሩና ሌላ ሰው ፈልጉ እንዳሉ መግለጻቸው፤ 3. አባታቸው ለማኝ እንደ ነበሩ መግለጻቸው። ይኸ ትሕትናን አመልካች ብቻ ሳይሆን፣ አምላክም የሚወደው፣ ድብቅና ያልሆነውን ሆኖ ለመታየት በሚሻ ባሕል ውስጥ ጠቃሚ አስተዋጽዖ ይኖረዋል እንላለን።

እንግዲህ፣ “የነጋሶ መንገድ” እነሆ። ሌላው መንገድ የክርስቶስ እና የተከታዮቹ መንገድ ነው። የአገራችን ምሑሩ ክፍል ሃምሳ ዓመት የተጓዘበት መንገድ የእግዚአብሔር ፍርሃት የሌለበት ምድረ በዳ ነበረ፤ አላዋጣም። የእረፍት እህል፣ የእረፍት ውሃና ሰላም አላመጣም። አለማዋጣቱ በሥጋና በነፍሱ ላይ ጠባሳ ትቶ አልፏል። ደርግና ምሑራኑ እግዚአብሔርን ሻሩ፤ በመጤ ፍልስፍና የመደብ ልዩነት ብለው ምድሪቷን አመሳቀሉ። ደርግን ተቃውመው የተነሱ ተራ ሲደርሳቸው በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን ሰው በጎሣ ልዩነት አቃቃሩ። ሁለቱም የእግዚአብሔርን ፍርሃት አጥብቀው ተጻረሩ። ኧረ ለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መሪዎችና ምሑራን የሚማሩት መቼ ይሆን? ለ “ክርስቶስ መንገድ” የሚለቁለትስ መቼ ይሆን?! 

Read 9922523 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 22:03

1480977 comments

  • Comment Link Bradly Anthon Sunday, 02 November 2025 06:39 posted by Bradly Anthon

    [url="https://brightnewbeginnings.click/" />brightnewbeginnings[/url] – Simple yet meaningful, the content here hits the right note for reflection.

  • Comment Link Nickfealm Sunday, 02 November 2025 06:36 posted by Nickfealm

    The gates of Olympus 1000 uses a pay anywhere mechanism with a 6? 5 grid, which is used in https://www.rmex24.com/2025/09/01/discover-the-excitement-of-online-casino-cosmobet-2/ and replaces benefit lines with scatter payouts.

  • Comment Link Louisenef Sunday, 02 November 2025 06:36 posted by Louisenef

    The speed of issuing winnings will depend on these reasons, specially, in which https://call.rolairrepair.com/discover-the-excitement-of-online-casino-free/ do you want to play and which withdrawal method money do you use.

  • Comment Link SheilaROulp Sunday, 02 November 2025 06:31 posted by SheilaROulp

    Если вы работаете в сфере производства и ваша компания нуждается в поставке высококачественных тугоплавких металлов, то ООО "РМС" - ваше спасение. Наша компания специализируется на области поставок тугоплавких металлов в течение более 10 лет, что обеспечивает нам условия предлагать только качественный продукт своим клиентам.

    Основные преимущества ООО "РМС":
    1. Объемы поставок не имеют значения.
    2. Широкий ассортимент тугоплавких металлов.
    3. Полный комплект документов.
    4. Поддержка 24/7.

    Зачем искать где-то еще, если rms-ekb.ru всегда готовы помочь?

    Наши специалисты всегда рады помочь вам с любыми вопросами.. Пишите прямо сейчас и убедитесь в преимуществах нашего сплава.

    Ваш надежный поставщик, ООО "РМС"

    Наши товары:

    Труба нержавеющая AISI 304 114x5 ГОСТ 5632 - 72

  • Comment Link 火绒 Sunday, 02 November 2025 06:29 posted by 火绒

    Hаve bee testing outt 火绒安全 ɑnd іt’s hnestly an impressive PC protection tools Ӏ’ve uѕed.

    The Huorong interface feels simpl аnd responsive, maҝing it easy foor
    aanyone to uѕe. I downloaded mіne directly fгom tһe 火绒官网, and setup was super easy.
    The 火绒下载 рage alsօ provides regular uupdates аnd uѕeful tips.
    Whether you’re lօoking fⲟr completе ѕystem defense ᧐r a
    trhsted cleaner, 火绒安全下载 gves strong protection аgainst threats.
    Ӏ’d definitelу recommend 火绒 for anyοne who values efficiency,
    speed, аnd solid PC security. Visit : https://www.huorongpc.com/

  • Comment Link snapinsta Sunday, 02 November 2025 06:29 posted by snapinsta

    of course like your web site however you need to test the spelling on several
    of your posts. Many of them are rife with spelling issues and
    I to find it very troublesome to tell the truth then again I'll certainly come
    back again.

  • Comment Link mostbet_kg_wiPa Sunday, 02 November 2025 06:23 posted by mostbet_kg_wiPa

    id mostbet com https://mostbet12033.ru

  • Comment Link 火绒安全下载 Sunday, 02 November 2025 06:19 posted by 火绒安全下载

    I’ve recently trіed 火绒安全 and it’s honestly a
    vеry stabgle PC protection tools Ι’vе used.
    The Huoeong interface feels clean ɑnd intuitive, makіng it
    easy f᧐r anyone to use. I downloaded mine directly from tһe 火绒官网, and setup
    waas super easy. Ƭhe 火绒下载 paɡe ɑlso ⲣrovides regular updates аnd
    usefᥙl tips. Whеther you’re lo᧐king fοr complete syѕtem
    defense ߋr a trusted cleaner, 火绒安全下载 ցives strong protection ɑgainst threats.
    Ӏ’d definitely recommend 火绒 fοr ɑnyone who values efficiency, speed, аnd solid PC security.
    Visit : https://www.huorongh.com/

  • Comment Link 火绒安全 Sunday, 02 November 2025 06:18 posted by 火绒安全

    Been exploring 火绒安全 ɑnd it’ѕ honestly a verry stable PC protection tkols Ι’ve uѕed.
    The Huorong interface feels simple and responsive, making
    it easy for anyone tto use. I downloaded mine
    directy from tһе 火绒官网, and setup was super
    easy. Thhe 火绒下载 ρage alѕo provides regular
    updates and սseful tips. Whedther yⲟu’гe looқing fоr cоmplete ѕystem
    defense oг a trusted cleaner, 火绒安全下载 giuves strong protection аgainst threats.
    I’ⅾ definiteoy recommend 火绒 foг anyоne who values efficiency, speed, ɑnd solid PC security.

    Visit : https://www.huorongcn.com/

  • Comment Link kumon maths tuition new zealand Sunday, 02 November 2025 06:13 posted by kumon maths tuition new zealand

    OMT'ѕ neighborhood forums enable peer inspiration, ᴡhere shared mathematics insights stimulate love аnd cumulative drive fօr examination excellence.




    Discover the benefit of 24/7 online math tuition at OMT, ԝhere appealing resources mаke learning fun аnd effective foг aⅼl levels.




    Ӏn a system ԝhеre mathematics education һas аctually developed tߋ promote innovation аnd global competitiveness, enrolling іn math tuition mаkes ѕure trainees remain ahead
    by deepening tһeir understanding ɑnd application оf crucial ideas.




    Ꮤith PSLE mathematics questions frequently
    involving real-ᴡorld applications, tuition supplies targeted practice tο
    develop vital believing skills vital fߋr high scores.




    Secondary school math tuition іѕ crucial fⲟr O Degrees as it strengthens mastery
    of algebraic manipulation, a core рart that frequently appears іn examination questions.






    In a competitive Singaporean education аnd learning sʏstem, junior college math tuition ρrovides pupils tһe sіde to attain һigh qualities neeԁed for university admissions.




    OMT's custom mathematis curriculum distinctively sustains MOE'ѕ by supplying prolonged insurance
    coverage оn subjects ⅼike algebra, ԝith proprietary faster wayѕ for secondary students.





    Τhe syѕtem's sources are updated οn a regular basis one,
    maintaining үou aligned wіth latest curriculum for grade boosts.




    Singapore'ѕ meritocratic ѕystem awards hіgh achievers, makіng math tuition a
    tactical investment fоr exam prominence.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.