×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:18

ሌላው መንገድ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ግምገማ ድርሰት

ሌላው መንገድ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎቻችን ከተለምዶ ውጭ የሕይወት ታሪካቸውን በመጽሐፍ አሳትመው እያሠራጩ ነው። ይህ አዲስ ክስተት ነው፤ የሚደገፍ ነው። ማን እንደሆኑ፣ ምን እንደሠሩ አስረግጠን ሳናውቅና በሠሩት ሥራ ዙሪያ ሳንወያይ ያለፉ የሕዝብ መሪዎች ጥቂቶች አይደሉምና ተዘርፈናል፣ ቅርስ ባክኖብናል። የአገራችንን ታሪካዊ ወቅቶች በግለሰቦቹ እይታ አስታከን ማገናዘብ ብሔራዊ መብታችን ብቻ ሳይሆን፣ የተመሠረተውን በጎ ከመርሳት የተነሳ ስሕተቶች እንዳይደገሙ፣ ፍርሃትና አሉባልታ እንዳይገዙን ለመከላከል ጭምር ይጠቅማል። በዚህ አጋጣሚ የጄኔራል ታዬ ጥላሁን የሕይወት ታሪክ እስካሁን አለመጻፉ ያሳስበናል። በዚሁ ድረ ገጽ፣ ከእስር ተፈተው ወደ ክርስቶስ አማንያን ማሕበር ተቀላቅያለሁ ያሉት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ፣ አሁን የእውነትን መንገድ ለይተው አውቀዋልና ሁሉን ግልጽ አድርገው በመጽሐፍ እንዲያሠፍሩ ማሳሰባችን ይታወሳል። ሌሎች፣ በተለይ ሴቶች ካሉ እንደዚሁ።

የዛሬው ትኩረታችን፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ባለፈው ወር፣ “ዳንዲ - የነጋሶ መንገድ” በሚል ርእስ ባሳተሙት መጽሐፍ ላይ ስለ ሰማእቱ ቄስ ጉዲና ቱምሳ ባሠፈሩት ላይ ብቻ ይሆናል። በነገራችን ላይ፣ ዶክተር ነጋሶ በቤተክርስቲያን አካባቢ የሚታወሱት በምዕራቡና በደቡብ-ምዕራቡ የአገራችን ክፍል የወንጌል አገልጋይና መሪ የነበሩት የቄስ ጊዳዳ ሶለን [በ1969 ዓ.ም. በ 78 ዓመታቸው ሞቱ] ልጅ በመሆናቸው ነው። ዶክተሩ፣ በመጽሐፋቸው ውስጥ ስለ ፍትሕ፣ በእግዚአብሔርና በሕግ ፊት ስለ ሰው ልጆች እኩልነት፣ ስለ ነፃነት ይገደኛል፤ ለዚህም ስታገል ኖሬአለሁ የማለታቸው መሠረቱ ምን እንደ ሆነ መገመት አያዳግትም። አባታቸው ቄስ ጊዳዳ [“ጊዳዳ” ትርጓሜው፦ “ለሕዝብ የሚያነባ” ማለት ሲሆን] በወንጌል ምክንያት የተሰደዱና ቤተክርስቲያን በመትከል የታወቁ የእምነት ሰው ነበሩ። በተጨማሪ፣ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት አሳድገው ለአገር መሪነት ያበቋቸውን እንደ እነ ክቡር አቶ አማኑኤል አብርሃምን፣ አቶ መርኪና መጃን፣ ኦነሲሞስ ነሲብን መጥቀስ ይቻላል። በአፍሪቃ የነፃነት ትግል ውስጥ ደግሞ ስመ-ጥር የሆኑት እነ ኔሬሬ፣ ማንዴላ፣ ካውንዳ፣ ንኵሩማ፣ ወዘተ፣ ከወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት የፈለቁ ናቸው። የቤተክርስቲያን አስተዋጽዖ እንደ ቀላል ሊታይ አይገባም ማለት ነው።

በ “ነጋሶ መንገድ” ላይ፦ ደርግ፣ቄስ ጉዲና ቱምሳንየገደለው፣ “የኦሮሞ ነፃነት ግንባር [ኦነግ] ናቸው ብሎሲሆንደርግከወደቀበኋላደግሞየቄሱአስከሬንከጅምላመቃብርወጥቶበስርዓትበተቀበረበትጊዜደርግቄሱንየገደለውየሃይማኖትነፃነትንለማፈንነበር ተብሎየተነገረውን ትክክል አይደለም ብለዋል። ለዚህም ማስረጃቸውን እንደሚከተለው አቅርበዋል፦ 1969 .ቄስጉዲናለቤተክርስቲያንስራወደጀርመንሲመጡእግረመንገዳቸውንከኦነግመልእክትይዘውመጥተውነበር።መልዕክቱንለመንገርመጀመሪያዲማነገዎማስትሬትዲግሪውንእያጠናከነበረበትሴኔጋልወደጀርመንእንዲመጣአደረጉናከዚያፍራንክፈርትከእኔጋርተገናኙ።ለእሱየመጣውመልዕክትጀርመንሀገርቢሮበመክፈትየኦነግወኪልሆኖእንዲሰራየሚልነበር።እኔደግሞዲማንእንድረዳነበርየተፈለገውሌላውቄስጉዲናየሰጡኝመረጃኦነግበመካከለኛውምስራቅአንድልዑክእንደሚልክናልዑኩበባሮቱምሳእንደሚመራየሚጠቁምነበር ቄስጉዲናንለመጨረሻጊዜያገኘኋቸውያኔነው።ደርግ፣ሀገርቤትሲገቡእስርቤትአስገብቶገደላቸውናከሌሎችጋርበጅምላተቀበሩ…” [ገጽ 110]።

ዶክተር ነጋሶ ማስረጃ ብለው ያቀረቡት አከራካሪ አይሆንም። ደርግ ቄስ ጉዲናን የገደለው ኦነግ ናቸው በሚል ሰበብ ነው። ይህን ስንል፣ ደርግ የወሰደው የግድያ እርምጃ ሆነ ያቀረበው ሰበብ ትክክል ነው ማለት አይደለም። ቄስ ጉዲናን በኦሮሞነታቸው ወይም በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ ፈርጆ ማለፍ ግን የኖሩለትንና የተሠውለትን የሕይወት ምስክርነት ማጕደፍ ይሆናል። ግለሰቡ ቁመተ-ረጂም፣ ከሠፈር ያለፈ ሰፊ አእምሮ የተለገሳቸው ነበሩና። ዶክተር ነጋሶ ይህን የሚክዱ አይመስለንም። በሌላ አነጋገር፣ የክርስቶስ ተከታይና የቤተክርስቲያኑ መሪ እንደሆኑ ከግምት ውስጥ ሳናስገባ ቄስ ጉዲናን ጠንቅቀን መረዳት አዳጋችና አሳሳች ይሆናል። ደርግ፣ ቄስ ጉዲናን የገደልኩት የቤተክርስቲያን መሪ በመሆናቸው ነው ሊል እንደማይችል ግልጽ ይመስለናል። በቤተክርስቲያን ላይ ስደት እና በአማንያን ላይ እስራት በታወጀበት ሰዓት የአምልኮ ነፃነት አለ አልልም ማለታቸው፤ ቀይና ነጭ ሽብር በየአውራ መንገዱ ያፈሰሰው ደም ሳይደርቅ እንዲህ የመሰለ አቋም መውሰድ ምን እንደሚያስከትል ለማንም ግልጽ ነው። በዚህ ላይ ወንድማቸው ባሮ ቱምሣ የአንጃ ፖለቲካ ፓርቲ መሪ ናቸው።

ቄስ ጉዲና የተሠውት በ 1971 ዓ.ም. በሃምሳ ዓመታቸው ነው። አመለካከታቸው ከጎሣና ከዘር ያለፈ ነው ስላልን መድገም አያሻንም። ጽሑፋቸውን ያነበበና ንግግራቸውን ያደመጠ ማንም እንደሚያውቀው ወንጌልን ከማሕበራዊ ፍትኅ ጋር አገናዝበው ማየት የተቻላቸው ግለሰብ ነበሩ። የክርስቶስን ወንጌል በቤተክርስቲያን ክልል መወሰን ወይም በማሕበረ ሰብ ጠርዝ ላይ መትከል፣ የወንጌልን “ብርሃን እና ጨው” ነት አለማጤን እንደሆነ የተረዱ መሪ ነበሩ። ለመንግሥት ሥጋት የሆኑት ከዚህ አመለካከታቸው የተነሳ ነው። ስለ ሰው ማንነት ያላቸው መረዳት ከወንጌል አስተምርሆ የመነጨ እንጂ ከሰብዓዊነት አመለካከት ብቻ የፈለቀ አልነበረም። ወንጌል፣ ሰው በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠሩን፣ ከዚህ የተነሳ ክቡር መሆኑን፣ በአዳማዊ ኃጢአት ምክንያት ከፈጣሪው፣ ከራሱ፣ ከባልጀራውና ከፍጥረት ሁሉ ጋር መቆራረጡን ያስተምራል። ይህም ከማርክሳዊ አመለካከት፣ ብርሃን ከጨለማ እንደሚለይ ይለያል። ወንጌል፦ ሰው ቁስ ብቻ ሳይሆን፣ ነፍስም መንፈስም ነው፤ በሥጋ በተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በኩል ከአምላኩ፣ ከራሱና ከሌላው ጋር የሚታረቅበት መንገድ ተዘጋጅቶለታል ይላል። እንግዲህ፣ እግዚአብሔርን ያላማከለ አመለካከት ሰውን ከኢኮኖሚያዊና ከማሕበራዊ ግንኙነቶቹ ነጥሎ ማየት እንደሚሳነው በደርግና አሁን በሚገዛው መንግሥታት የታየው አመራር በቂ ማስረጃ የሚሆን ይመስለናል።

ቄስ ጉዲና በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶች ማንበብና መጻፍ እንዲስፋፋ ከወጠኑትና ጥረት ካደረጉት መካከክል የመጀመሪያው ናቸው። አብዮት ከመፈንዳቱ በፊት፣ ማሕበራዊ ነውጥ ተቃርቧል፣ ቤተክርስቲያን መዘጋጀት አለባት ሲሉ እንደ ነበረ የሰሙ ዛሬም በሕይወት አሉ። ደርግ ሥልጣን ሲይዝ፣ ጸረ-ሃይማኖት/ጸረ-ክርስቲያን መመሪያ እንደሚያውጅ፣ ለዚህም ሥርዓት መበገር እንደማይገባ ጠንቅቀው ተረድተው ነበር። ንጉሥ ቢሆን፣ የፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር፣ የክርስቶስን ጌትነት ለሚቀናቀን ለማናቸውም ምድራዊ ሥልጣን ማጎንበስ አይገባም ይሉ ነበር።

ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው በምድር በሰማይ

እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዶክተር ነጋሶ ስለ ቄስ ጉዲና የነገሩን አዲስ ነገር የለም። ቄስ ጉዲና ኦሮሞ መሆናቸው፣ የመጣው ለውጥ ከአብራኩ ለወጡት ሕዝብ ያስገኘው ጥቅም አንሶ እያዩ ዝም አለማለታቸው እንደ ድንቅ ሊታይ አይገባም።  ዶክተር ነጋሶም እኮ ኦሮሞ ናቸው። ኦሮሞ ስለሆኑ፣ የሚታገሉት ለኦሮሞ ሕዝብ ብቻ ነው ማለት ታዲያ የትግላቸውን ፈር ባጭር አያስቀርም? ያስቀራል እንጂ። አያስቀርም ብንል፣ በመጽሐፋቸው ላይ እንደ ተመለከተው ለዲሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነትና ለሰብአዊ መብት መከበር ያደረጉት አስተዋጽዖ ያግደናል። ስለ ቄስ ጉዲና ግን ሊዘነጋ የማይገባ ጉዳይ፣ ደርግ በፍትኅ ስም የሚያካሄደውን ግድያና በደል አይተው ዝም አለማለታቸውና አለመተባበራቸው ነው። እኚህን ሰው በአንድ አንጃ መከለል አግባብ አይሆንም የምንለው ለዚህ ነው። የሰውን ሞላ ነፃ የሚያወጣውን የክርስቶስን ፍትሓዊ ወንጌል አቋማቸው ቢያደርጉ ድንቅ አይደለም ማለት ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዶክተር ነጋሶ፣ ኦነግ ናቸው ብለው ያቀረቡት ማስረጃ፣ ቄስ ጉዲና የክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪ ከመሆናቸውና ዘርና ጎሣ ከማይወስነው ፍትኀዊ ወንጌል አራማጅነታቸው አንዳች እንደማይቀንስ ነው። ባጭሩ፣ የጉዲናን ስነመለኮታዊና ማሕበራዊ አቋም መነጣጠል ሐቅን ማዛባትና የሌለ ስም መስጠት ይሆናል። 

መንግሥታት ሁሉ የሚቀናቀናቸውን ለማስወገድ የሚጠቀሙበት ዘዴ ተመሳሳይ ነው። የአሜሪካ መንግሥት፣ እ.አ.አ በ1968 ዓ.ም. የሰብአዊ መብት ተሟጋች የነበረውን ቄስ ማርቲን ሉተር ኪንግን [በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] የገደለው ኮሚዩኒስት ብሎ ነው። ማርቲን ኪንግ የአገሩን ዘረኛ ፖሊሲ መቃወሙ ብዙ ችግር አስከትሎበታል፤ የራሱና የቤተሰቡ ሕይወት እለት እለት ለአደጋ የተጋለጠ ነበር። የፍጻሜ እርምጃ የተወሰደበት ግን ከቤተክርስቲያን ክልል ወጣ ብሎ፣ አሜሪካ በቪዬትናም ስለምታካሄደው ሕገ ወጥ ጦርነት እና፣ በተለይም በኢኮኖሚ ረገድ በጥቁሮች ላይ የሚካሄደውን አድልዎና ግፍ መቃወምና ወደ ሰሜኑ የአሜሪካ ግዛት ዘልቆ ማደራጀት በጀመረበት ወቅት ነበር። ወንጌል ሙሉ የሚሆነው፣ ቤተክርስቲያን ነፍሳትን ወደ ክርስቶስ መንግሥት ከማምጣት ጋር ለማሕበራዊ ፍትኅ ስትታገል ጭምር ነው። ይህም ከፍተኛ መስዋእት ይጠይቃል፤ ፍሬው ደግሞ በደም ይደረጃል።

የጀርመን መንግሥት ቄስ ዲትሪኽ ቦንኦፈር [እ.አ.አ. በ1945 ዓ.ም. በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] እውነተኛዪቱ ቤተክርስቲያን፣ ይሁዲና ጂፕሲዎች እየታደኑ ባለበት ሰዓት፣ ማሕበረ ምእመኑን እንዳያስተምር አሳቡን በጽሑፍ እንዳያሠፍር በማገዱ ሂትለርን ለማስወገድ ከተደራጁት ጋር ለማበር ተገደደ። ያኔ ለቦንኦፈር ጥያቄ የሆነበትና ዛሬም ለኛ ጥያቄ ሊሆን የሚገባው፣ እንዴት ከተመረዘ ማሕበራዊ ሥርዓት ውስጥ ራስን ማዳን ይቻላል የሚለው ሳይሆን፣ የሚቀጥለው ትውልድ እንዴት ይሆናል? እንዴትስ ይኖራል? የሚለው ነው። ቦንኦፈር አሜሪካ ሄዶ በዚያው መቅረትና ተደላድሎ መኖር ሲችል፣ የሚያውቁት ሁሉ ‘አትሂድ፣ ችግሩ ይለፍ’ ሲሉት እምቢ ብሎ ወደ ትውልድ ምድሩ ወደ ጀርመን አገር የተመለሰው ሊገደል እንደሚችል ሳይጠረጥር ቀርቶ አይደለም።

የኢጣልያ ፋሺስት አቡነ ጴጥሮስን [በ 1928 ዓ.ም. በ 54 ዓመታቸው ተሠው] ገና አገራችንን እንደ ወረረ ወዲያው ያስገደለው አላስቀምጥ አላስተኛ ስላሉ ነው፤ ሕዝቡን ለአረመኔ ወራሪ አልገዝትም፣ የተቀበልኩትን የወንጌል አደራና ሕዝቡን አሳልፌ ከምሰጥ ብሠዋ ይሻለኛል ስላሉ ነው። ለሕይወታቸው አልሳሱም።

ቄስ ጉዲና፣ ቄስ ማርቲን፣ ቄስ ቦንኦፈር እና አቡነ ጴጥሮስ በተገኙበት ሰማእታት ናቸው። ሁሉም የወጡት ከክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው። የሞቱት በወንጌል ዓላማ ለፍትኅ ነው። በመጨረሻዋ ሰዓት የተናገሩትን ቃል ማገናዘብ ደግሞ የሕይወታቸውን ጥሪና ቁምነገር ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። ሰው ወደ ሞት ሲቃረብ የሚናገረው ከሌላው ጊዜ ይልቅ ተኣማኒነት ይኖረዋልና። ለዚህም ነው ወደ ሞት ለተቃረበ ሰው፦ ምን የምትለው ነገር አለህ? ተብሎ የመጨረሻ እድል የሚሰጠው።

ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ፣ በፋሺስት ገዳዮች ፊት ቆመው፦ “ሥጋንም የሚገድሉትን፣ ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ …” እያሉና ሕዝቡ እጁን እንዳይሰጥ እየመከሩ በጥይት ተደብድበው ሞቱ። ይህም፣ “ለጊዜው፣ በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ” የሚለውን ሐዋሪያዊ ቃል ያስታውሰናል [ማቴዎስ 10:28 እና ወደ ዕብራውያን 11:25]።

ማርቲንኪንግ የተጋበዘበት የምሽት ፕሮግራም ከመድረሱ በፊት፣ ሙዚቃ እንዲጫወት ለተመደበው ሰው፣ “ውድ ጌታ [ኢየሱስ] …እጄን ያዘኝ” የምትለዋን ዝማሬ ጥሩ አድርጎ እንዲጫወታት ደጋግሞ ጠይቆት ነበር። ቦንኦፈር ደግሞ፣ “እነሆ ፍጻሜው ደረሰ፣ ለኔ ግን የሕይወት ጅማሬ ነው” ብሎ ተንበርክኮ ከጸለየ በኋላ ተሰቀለ።

ለቄስ ጉዲና፣ “… እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ” የሚለው ቃል መመሪያቸው እንደነበር ተዘግቧል [2ኛ ቆሮንቶስ 5:15]። ተይዘው በተገደሉበት ምሽት፣ በኡራዔል መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ኢየሱስን ከሰበኩ በኋላ ኢየሱስን እያሰቡ ደጅ ወጡ። በጨለማ ተገን አፍነው ገደሏቸው። ነፍሳቸው ግን ወደ ዘላለሙ ብርሃን፣ የዓለም ብርሃን ወደ ሆነው ወደ ኢየሱስ አገር አመለጠች። ሃሌ ሉያ!

ታዲያ፣ አንድን ግለሰብ ሰማእት ነው የሚያሰኘው ምንድነው? ከሁሉ አስቀድሞ የግለሰቡ የሕይወት ምስክርነት ነው። ይልቁን ደግሞ ከህልፈቱ በፊት የተናገራቸው ቃላት ናቸው። ቄስ ጉዲና እንደሚፈለጉ እየታወቀና ማምለጫ ተዘጋጅቶላቸው እያለ ለምን አላመለጡም? ታስረው መፈታታቸው ማስጠንቀቂያ ሳይሆናቸው ቀርቶ ነው? ምሥጢሩ፣ ራሳቸውን የቤተክርስቲያኑ እረኛ ከሆነው ከኢየሱስ በታች የመንጋው እረኛ መሆናቸውን ጠንቅቀው የተረዱ ሰው ስለነበረ ነው። በታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ አማላጅነት ከእስር ተፈትተው፣ ከአገር እንዲወጡ አሳብ ሲቀርብላቸው፦ “እኔ የቤተክርስቲያን መሪ ሆኜ ሳለ፣ እንዴት በፈተና ሰዓት መንጋውን ትቼ እሸሻለሁ? ደግሞስ፣ ካህናቱን የትም አትሂዱ ብዬ እየተማፀንኳቸው ልሸሽ? አልሸሽም፣ አላደርገውም” ብለው ነበር የመለሱት። “መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል፣ በጎቹም ይበተናሉ” [ዮሐንስ 10:12]።

የ”ነጋሶ መንገድ” ይህን ዋነኛ ስነ መለኮታዊ መረዳት የዘነጋው ይመስላል። ምናልባት መጽሐፉ የተጻፈው ከዚህ አኳያ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል። ወቅቱ በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ላይ መንግሥት የስደት እና የእሥራት ዘመቻ የሚያካሄድበት ሰዓት ነበር። ቄስ ጉዲና የሚመሩት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ደግሞ ብዙ እንቅስቃሴዋ በውጭው ዓለም እና በምዕራብና ደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ መሆኑ፣ የኦነግ መሪዎችም [ዶክተር ነጋሶን ጨምሮ] አብዛኛዎቹ ከቤተክርስቲያንና ከዚሁ ክፍለ ሃገር የወጡ መሆናቸው ለመንግሥት ሥጋት ፈጥሮ ነበር። ከዚህ የተነሳ ቤተክርስቲያንና መሪዎቿን በዐይነ ቁራኛ መከታተል ግድ ሆነ፤ አድራጎቱም፣ የመንግሥትን ኢፍትኀዊ አመራር አደባባይ አወጣው።

ከዚህ መጽሐፍ ጋር በተያያዘ አንድ የሚከነክነንን ጉዳይ እናንሳና እንጨርስ። ለመሆኑ፣ የአገራችን ምሑራን ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ዘላቂ የሆነ ምን ማሕበራዊ አስተዋጽኦ ወይም መፍትሔ አስገኝተዋል? በመደብና በጎሣ ሕዝቡን ከፋፍለው አለመተማመንን ዘርተውበታል፤ ይህን አይተናል። ያውቃሉ የተባሉት እርስ በርስ መስማማት ሆነ መከባበር ተስኖአቸዋል። አገሪቷን ወዴት መምራት እንደሚገባቸው ገና እርግጠኞች አይደሉም፤ የሌሎችን አሳብ ለመስማት አይፈቀዱም። የጋራ በሆነች አገር፣ ያልተስማማቸውን የማግለልና የማውገዝ ባሕል ተጠናውቶአቸዋል። ይህንና ያን ሲሉ ስንት ትውልድ ፈጁ፤ በሙከራ ብቻ ምድሪቷን አስረጁ። ቤተክርስቲያንን ከሚያፈርስ፣ ፈርሃ እግዚአብሔርን ከሚሸረሽር አድራጎት ሊቆጠቡ አልቻሉም። ቤተክርስቲያንን ለዓላማቸው ከመጠቀም አልቦዘኑም። የክርስቶስን ወንጌል ከባህል፣ ከአፈ-ታሪክና ከጎሠኛ አስተሳሰብ ለይተው ስለማያዩ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑን ያምሳሉ። “እግዚአብሔር የለም” ያሉንና ሊያሰኙን ያንገላቱን ዛሬ ወዴት አሉ? የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ግን ዛሬም አለች፣ ጌታዋ ሕያው ስለሆነ፣ ሕያው ነች። እግዚአብሔርን የማይፈሩ፣ እግዚአብሔር የማያይ የመሰላቸው ሕዝብን ሲበድሉና ሲያንገላቱ፣ ለወገኔ ይጠቅማል ማለት ሲያበዙ፣ የምሕረት እጁን ስለ ዘረጋ እንጂ፣ ዝምታው ስለማይፈርድ አለመሆኑን አላስተዋሉም። እግዚአብሔር ሳ-ይ-ፈ-ራ ሕዝብ አይዋደድም፤ እግዚአብሔር ሳይከበር ሕዝብ አይከበርም፤ አይከባበርም።

“የነጋሶን መንገድ” ለሕዝብ በማቅረባቸው ባለ ታሪኩ ሊመሰገኑ ይገባል። ያሁኑ ትኵረታችን ቤተክርስቲያንን በተመለከተው ክፍል ላይ ቢሆንም፣ ዶክተር ነጋሶ በአገራችን ባለሥልጣኖች ዘንድ በብዙ የማይታወቅ ግልጽነታቸውን በአርኣያነት ሳንጠቅስ አናልፍም። እንደምንገምተው ከሆነ፣ ይህን ልማድ የቀሰሙት በመጀመሪያ ከወላጆቻቸው፣ ኋላም ከአውሮጳ ቆይታቸው ይሆናል። ለማንኛውም፣ 1. የአገር መሪ በሕይወት እያለ ከሥልጣን ወርዶ በሕዝብ መካከል እንደ ተራ ዜጋ መኖር፤ 2. የአገራችን ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በተጠየቁ እለት እንደ ፈሩና ሌላ ሰው ፈልጉ እንዳሉ መግለጻቸው፤ 3. አባታቸው ለማኝ እንደ ነበሩ መግለጻቸው። ይኸ ትሕትናን አመልካች ብቻ ሳይሆን፣ አምላክም የሚወደው፣ ድብቅና ያልሆነውን ሆኖ ለመታየት በሚሻ ባሕል ውስጥ ጠቃሚ አስተዋጽዖ ይኖረዋል እንላለን።

እንግዲህ፣ “የነጋሶ መንገድ” እነሆ። ሌላው መንገድ የክርስቶስ እና የተከታዮቹ መንገድ ነው። የአገራችን ምሑሩ ክፍል ሃምሳ ዓመት የተጓዘበት መንገድ የእግዚአብሔር ፍርሃት የሌለበት ምድረ በዳ ነበረ፤ አላዋጣም። የእረፍት እህል፣ የእረፍት ውሃና ሰላም አላመጣም። አለማዋጣቱ በሥጋና በነፍሱ ላይ ጠባሳ ትቶ አልፏል። ደርግና ምሑራኑ እግዚአብሔርን ሻሩ፤ በመጤ ፍልስፍና የመደብ ልዩነት ብለው ምድሪቷን አመሳቀሉ። ደርግን ተቃውመው የተነሱ ተራ ሲደርሳቸው በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን ሰው በጎሣ ልዩነት አቃቃሩ። ሁለቱም የእግዚአብሔርን ፍርሃት አጥብቀው ተጻረሩ። ኧረ ለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መሪዎችና ምሑራን የሚማሩት መቼ ይሆን? ለ “ክርስቶስ መንገድ” የሚለቁለትስ መቼ ይሆን?! 

Read 10446969 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 22:03

1530609 comments

  • Comment Link Uazrrwr Monday, 12 January 2026 02:22 posted by Uazrrwr

    Заказать диплом любого университета. Изготовление диплома занимает минимум времени, а стоимость - невысокая. В результате вы сможете сберечь бюджет и получить работу мечты. Приобрести диплом можно используя сайт компании. - c3tservices.ca/companies/diplomx-grups

  • Comment Link DoctorlazutaLak Monday, 12 January 2026 02:22 posted by DoctorlazutaLak

    промокод озон ноябрь на скидку http://jktroickiy.forumex.ru/viewtopic.php?f=2&t=18075 прогоны влияют на позиции сайта http://nrj.rs.ba/viewtopic.php?p=85013#p85013 прогон по траст сайтам https://forum.l2astral.org/viewtopic.php?p=460409#p460409 ускоренная индексация сайта онлайн

    прогон сайта по каталогам это промокод kfc 2022 на скидку на заказ http://haudyhome.com/bbs/board.php?bo_table=free&wr_id=2165871 самостоятельный прогон сайта http://baljuvon.tj/index.php?subaction=userinfo&user=obtainablecampe промокод на скидку убер https://vi.be/platform/upholsteredfurniturerendering

    продвижение в маркетинге статья сайт прогонов индексирование страницы запрещено тегом noindex https://forum.expert-watch.com/index.php?action=profile;u=186180 винлаб промокод на скидку http://www.pc28lt.com/space-uid-313857.html

    официальный бездепозитный бонус casino http://liuwenzheng.com.cn/home.php?mod=space&uid=866263&do=profile прогоны трастовых сайтов аквапарк питерлэнд купоны на скидку https://paladinscounter.com/users/GlennBal каталоги для прогона сайтов http://cmsthemefinder.com/userinfo.php?uid=41077#

    прогон сайта форум http://forum.moto-fan.pl/uzytkownik-parsimoniousbul биглион новосибирск купоны на скидку снежная королева промокод на скидку https://images.google.com.pk/url?sa=t&url=https://doctorlazuta.by/ купоны на скидку санкт петербург http://msfo-soft.ru/msfo/forum/messages/forum26/topic22584/message471001/?result=new#message471001

    заказать прогон по трастовых сайтов http://n98077fz.bget.ru/users/overjoyedidol76 купон на скидку использовать http://zhwbn.com/bbs/space-uid-159199.html мореон аквапарк купоны на скидку https://forum.wapinet.ru/profile.php?id=7803 прогон сайта 2020

    бездепозитные бонусы деньгами игровые автоматы http://ww.daejinmc.net/bbs/board.php?bo_table=free&wr_id=18951 дата индексации страницы https://popcporn.net/user/GeraldAdoky/ аквапарк купоны на скидку спб http://nyjbrc.com/free/30563 сервис прогона сайта к

    теремок купоны на скидку москва https://www.red-bookmarks.win/making-the-most-of-take-advantage-of-wholesale-bag-purchases прогон трастовых сайтов http://b775218w.bget.ru/user/JefferyOpify/ карибия купоны на скидку 2022 https://king-wifi.win/index.php?title=Crazy_Time:_casino_en_vivo,_RTP_y_demo_para_Chile_y_LATAM большая перемена купон на скидку видео купон на скидку

    http://budennovsk-ims.ru/bitrix/click.php?goto=https://doctorlazuta.by

  • Comment Link Jarioruoo Monday, 12 January 2026 02:20 posted by Jarioruoo

    Приобрести диплом университета!
    Наша компания предлагаетвыгодно приобрести диплом, который выполняется на оригинальной бумаге и заверен мокрыми печатями, водяными знаками, подписями. Наш документ способен пройти лубую проверку, даже при помощи специального оборудования. Достигайте своих целей быстро и просто с нашим сервисом- onestopclean.kr/bbs/board.php?bo_table=free&wr_id=828117

  • Comment Link math tuition singapore Monday, 12 January 2026 02:18 posted by math tuition singapore

    Visual aids in OMT's curriculum mɑke abstract concepts substantial,
    cultivating а deep recognition fоr mathematics and motivation tⲟ conquer exams.





    Join ߋur small-groսp оn-site classes іn Singapore fоr individualized guidance іn a nurturing environment that constructs strong foundational mathematics abilities.




    Singapore'ѕ wօrld-renowned math curriculum highlights conceptual understanding օver
    simple computation, making math tuition іmportant fⲟr students tо grasp deep ideas
    ɑnd stand ߋut in national tests ⅼike PSLE and O-Levels.





    With PSLE math questions frequently including real-ԝorld applications, tuition ⲟffers targeted
    practice tо establish critical believing abilities essential fߋr
    high ratings.



    Witһ O Levels stressing geometry proofs ɑnd theses, math tuition рrovides specialized drills tⲟ ensure trainees can take on tһeѕe ᴡith accuracy аnd confidence.





    With A Levels requiring efficiency in vectors ɑnd complex numbers, math tuition supplies targeted
    technique tⲟ deal wіtһ these abstract ideas properly.




    OMT'ѕ special technique іncludes a syllabus tһat complements tһe MOE structure with
    joint components, encouraging peer conversations ߋn mathematics principles.




    OMT'ѕ on tһе internet tuition iѕ kiasu-proof leh, offering yⲟu that aԀded edge
    to outmatch in O-Level mathematics examinations.




    Math tuition motivates ѕelf-confidence via success іn tiny turning points, driving
    Singapore trainees tоwards gеneral exam victories.

  • Comment Link vipryamitel dyson kypit_insl Monday, 12 January 2026 02:16 posted by vipryamitel dyson kypit_insl

    dyson выпрямитель купить в москве dyson выпрямитель купить в москве .

  • Comment Link Manuel Monday, 12 January 2026 02:16 posted by Manuel

    https://matters.town/a/oawp7c0hh19w

  • Comment Link vipryamitel daison kypit_ecmr Monday, 12 January 2026 02:15 posted by vipryamitel daison kypit_ecmr

    выпрямитель для волос dyson airstrait ht01 выпрямитель для волос dyson airstrait ht01 .

  • Comment Link Uazrkgg Monday, 12 January 2026 02:14 posted by Uazrkgg

    Приобрести диплом ВУЗа. Производство диплома занимает немного времени, а стоимость при этом невысокая. В итоге вы имеете возможность сберечь деньги и время и найти прекрасную работу вашей мечты. Заказать диплом на заказ в Москве можно через официальный сайт компании. - key2yards.com/author/glorybernhardt

  • Comment Link jc 1 math tuition Monday, 12 January 2026 02:12 posted by jc 1 math tuition

    The caring environment at OMT motivates inquisitiveness
    іn mathematics, transforming Singapore trainees іnto passionate students encouraged tߋ accomplish leading
    test results.



    Discover tһe benefit ߋf 24/7 online math tuition аt OMT, wһere engaging resources make finding out enjoyable ɑnd reliable fοr all levels.




    With math incorporated seamlessly іnto Singapore'ѕ classroom settings tο benefit b᧐th
    teachers and students, committed math tuition enhances tһese gainss bу offering tailored assistance fߋr continual achievement.




    Ꮤith PSLE mathematics concerns οften involving real-ԝorld
    applications, tuition ᧐ffers targeted practice tо establish critical
    believing skills essential fߋr һigh ratings.



    Thorоugh responses from tuition trainers οn method attempts
    helps secondary pupils pick սρ from mistakes, boosting precision fօr the
    actual O Levels.




    Preparing for the changability of Ꭺ Level questions, tuition establishes adaptive analytical techniques
    fⲟr real-time examination scenarios.



    Eventually, OMT'ѕ special proprietary curriculum complements tһе Singapore MOE
    educational program Ьy cultivating indxependent
    thinkers furnished f᧐r lifelong mathematical success.




    Endless access tߋ worksheets suggests ʏou exercise սntil shiok, enhancing
    yoᥙr mathematics ѕeⅼf-confidence and qualities in no time аt aⅼl.





    Math tuition influences ѕelf-confidence thгough success іn smаll turning pⲟints,
    driving Singapore pupils t᧐wards overall exam triumphs.

  • Comment Link Jariorymf Monday, 12 January 2026 02:12 posted by Jariorymf

    Заказать диплом о высшем образовании!
    Мы предлагаембыстро и выгодно купить диплом, который выполняется на оригинальном бланке и заверен мокрыми печатями, штампами, подписями. Диплом способен пройти лубую проверку, даже при использовании специальных приборов. Решите свои задачи максимально быстро с нашей компанией- git.jetplasma-oa.com/olivemorton832/1081106/wiki/Купить+диплом+Рѕ+среднем.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.