×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:18

ሌላው መንገድ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ግምገማ ድርሰት

ሌላው መንገድ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎቻችን ከተለምዶ ውጭ የሕይወት ታሪካቸውን በመጽሐፍ አሳትመው እያሠራጩ ነው። ይህ አዲስ ክስተት ነው፤ የሚደገፍ ነው። ማን እንደሆኑ፣ ምን እንደሠሩ አስረግጠን ሳናውቅና በሠሩት ሥራ ዙሪያ ሳንወያይ ያለፉ የሕዝብ መሪዎች ጥቂቶች አይደሉምና ተዘርፈናል፣ ቅርስ ባክኖብናል። የአገራችንን ታሪካዊ ወቅቶች በግለሰቦቹ እይታ አስታከን ማገናዘብ ብሔራዊ መብታችን ብቻ ሳይሆን፣ የተመሠረተውን በጎ ከመርሳት የተነሳ ስሕተቶች እንዳይደገሙ፣ ፍርሃትና አሉባልታ እንዳይገዙን ለመከላከል ጭምር ይጠቅማል። በዚህ አጋጣሚ የጄኔራል ታዬ ጥላሁን የሕይወት ታሪክ እስካሁን አለመጻፉ ያሳስበናል። በዚሁ ድረ ገጽ፣ ከእስር ተፈተው ወደ ክርስቶስ አማንያን ማሕበር ተቀላቅያለሁ ያሉት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ፣ አሁን የእውነትን መንገድ ለይተው አውቀዋልና ሁሉን ግልጽ አድርገው በመጽሐፍ እንዲያሠፍሩ ማሳሰባችን ይታወሳል። ሌሎች፣ በተለይ ሴቶች ካሉ እንደዚሁ።

የዛሬው ትኩረታችን፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ባለፈው ወር፣ “ዳንዲ - የነጋሶ መንገድ” በሚል ርእስ ባሳተሙት መጽሐፍ ላይ ስለ ሰማእቱ ቄስ ጉዲና ቱምሳ ባሠፈሩት ላይ ብቻ ይሆናል። በነገራችን ላይ፣ ዶክተር ነጋሶ በቤተክርስቲያን አካባቢ የሚታወሱት በምዕራቡና በደቡብ-ምዕራቡ የአገራችን ክፍል የወንጌል አገልጋይና መሪ የነበሩት የቄስ ጊዳዳ ሶለን [በ1969 ዓ.ም. በ 78 ዓመታቸው ሞቱ] ልጅ በመሆናቸው ነው። ዶክተሩ፣ በመጽሐፋቸው ውስጥ ስለ ፍትሕ፣ በእግዚአብሔርና በሕግ ፊት ስለ ሰው ልጆች እኩልነት፣ ስለ ነፃነት ይገደኛል፤ ለዚህም ስታገል ኖሬአለሁ የማለታቸው መሠረቱ ምን እንደ ሆነ መገመት አያዳግትም። አባታቸው ቄስ ጊዳዳ [“ጊዳዳ” ትርጓሜው፦ “ለሕዝብ የሚያነባ” ማለት ሲሆን] በወንጌል ምክንያት የተሰደዱና ቤተክርስቲያን በመትከል የታወቁ የእምነት ሰው ነበሩ። በተጨማሪ፣ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት አሳድገው ለአገር መሪነት ያበቋቸውን እንደ እነ ክቡር አቶ አማኑኤል አብርሃምን፣ አቶ መርኪና መጃን፣ ኦነሲሞስ ነሲብን መጥቀስ ይቻላል። በአፍሪቃ የነፃነት ትግል ውስጥ ደግሞ ስመ-ጥር የሆኑት እነ ኔሬሬ፣ ማንዴላ፣ ካውንዳ፣ ንኵሩማ፣ ወዘተ፣ ከወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት የፈለቁ ናቸው። የቤተክርስቲያን አስተዋጽዖ እንደ ቀላል ሊታይ አይገባም ማለት ነው።

በ “ነጋሶ መንገድ” ላይ፦ ደርግ፣ቄስ ጉዲና ቱምሳንየገደለው፣ “የኦሮሞ ነፃነት ግንባር [ኦነግ] ናቸው ብሎሲሆንደርግከወደቀበኋላደግሞየቄሱአስከሬንከጅምላመቃብርወጥቶበስርዓትበተቀበረበትጊዜደርግቄሱንየገደለውየሃይማኖትነፃነትንለማፈንነበር ተብሎየተነገረውን ትክክል አይደለም ብለዋል። ለዚህም ማስረጃቸውን እንደሚከተለው አቅርበዋል፦ 1969 .ቄስጉዲናለቤተክርስቲያንስራወደጀርመንሲመጡእግረመንገዳቸውንከኦነግመልእክትይዘውመጥተውነበር።መልዕክቱንለመንገርመጀመሪያዲማነገዎማስትሬትዲግሪውንእያጠናከነበረበትሴኔጋልወደጀርመንእንዲመጣአደረጉናከዚያፍራንክፈርትከእኔጋርተገናኙ።ለእሱየመጣውመልዕክትጀርመንሀገርቢሮበመክፈትየኦነግወኪልሆኖእንዲሰራየሚልነበር።እኔደግሞዲማንእንድረዳነበርየተፈለገውሌላውቄስጉዲናየሰጡኝመረጃኦነግበመካከለኛውምስራቅአንድልዑክእንደሚልክናልዑኩበባሮቱምሳእንደሚመራየሚጠቁምነበር ቄስጉዲናንለመጨረሻጊዜያገኘኋቸውያኔነው።ደርግ፣ሀገርቤትሲገቡእስርቤትአስገብቶገደላቸውናከሌሎችጋርበጅምላተቀበሩ…” [ገጽ 110]።

ዶክተር ነጋሶ ማስረጃ ብለው ያቀረቡት አከራካሪ አይሆንም። ደርግ ቄስ ጉዲናን የገደለው ኦነግ ናቸው በሚል ሰበብ ነው። ይህን ስንል፣ ደርግ የወሰደው የግድያ እርምጃ ሆነ ያቀረበው ሰበብ ትክክል ነው ማለት አይደለም። ቄስ ጉዲናን በኦሮሞነታቸው ወይም በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ ፈርጆ ማለፍ ግን የኖሩለትንና የተሠውለትን የሕይወት ምስክርነት ማጕደፍ ይሆናል። ግለሰቡ ቁመተ-ረጂም፣ ከሠፈር ያለፈ ሰፊ አእምሮ የተለገሳቸው ነበሩና። ዶክተር ነጋሶ ይህን የሚክዱ አይመስለንም። በሌላ አነጋገር፣ የክርስቶስ ተከታይና የቤተክርስቲያኑ መሪ እንደሆኑ ከግምት ውስጥ ሳናስገባ ቄስ ጉዲናን ጠንቅቀን መረዳት አዳጋችና አሳሳች ይሆናል። ደርግ፣ ቄስ ጉዲናን የገደልኩት የቤተክርስቲያን መሪ በመሆናቸው ነው ሊል እንደማይችል ግልጽ ይመስለናል። በቤተክርስቲያን ላይ ስደት እና በአማንያን ላይ እስራት በታወጀበት ሰዓት የአምልኮ ነፃነት አለ አልልም ማለታቸው፤ ቀይና ነጭ ሽብር በየአውራ መንገዱ ያፈሰሰው ደም ሳይደርቅ እንዲህ የመሰለ አቋም መውሰድ ምን እንደሚያስከትል ለማንም ግልጽ ነው። በዚህ ላይ ወንድማቸው ባሮ ቱምሣ የአንጃ ፖለቲካ ፓርቲ መሪ ናቸው።

ቄስ ጉዲና የተሠውት በ 1971 ዓ.ም. በሃምሳ ዓመታቸው ነው። አመለካከታቸው ከጎሣና ከዘር ያለፈ ነው ስላልን መድገም አያሻንም። ጽሑፋቸውን ያነበበና ንግግራቸውን ያደመጠ ማንም እንደሚያውቀው ወንጌልን ከማሕበራዊ ፍትኅ ጋር አገናዝበው ማየት የተቻላቸው ግለሰብ ነበሩ። የክርስቶስን ወንጌል በቤተክርስቲያን ክልል መወሰን ወይም በማሕበረ ሰብ ጠርዝ ላይ መትከል፣ የወንጌልን “ብርሃን እና ጨው” ነት አለማጤን እንደሆነ የተረዱ መሪ ነበሩ። ለመንግሥት ሥጋት የሆኑት ከዚህ አመለካከታቸው የተነሳ ነው። ስለ ሰው ማንነት ያላቸው መረዳት ከወንጌል አስተምርሆ የመነጨ እንጂ ከሰብዓዊነት አመለካከት ብቻ የፈለቀ አልነበረም። ወንጌል፣ ሰው በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠሩን፣ ከዚህ የተነሳ ክቡር መሆኑን፣ በአዳማዊ ኃጢአት ምክንያት ከፈጣሪው፣ ከራሱ፣ ከባልጀራውና ከፍጥረት ሁሉ ጋር መቆራረጡን ያስተምራል። ይህም ከማርክሳዊ አመለካከት፣ ብርሃን ከጨለማ እንደሚለይ ይለያል። ወንጌል፦ ሰው ቁስ ብቻ ሳይሆን፣ ነፍስም መንፈስም ነው፤ በሥጋ በተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በኩል ከአምላኩ፣ ከራሱና ከሌላው ጋር የሚታረቅበት መንገድ ተዘጋጅቶለታል ይላል። እንግዲህ፣ እግዚአብሔርን ያላማከለ አመለካከት ሰውን ከኢኮኖሚያዊና ከማሕበራዊ ግንኙነቶቹ ነጥሎ ማየት እንደሚሳነው በደርግና አሁን በሚገዛው መንግሥታት የታየው አመራር በቂ ማስረጃ የሚሆን ይመስለናል።

ቄስ ጉዲና በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶች ማንበብና መጻፍ እንዲስፋፋ ከወጠኑትና ጥረት ካደረጉት መካከክል የመጀመሪያው ናቸው። አብዮት ከመፈንዳቱ በፊት፣ ማሕበራዊ ነውጥ ተቃርቧል፣ ቤተክርስቲያን መዘጋጀት አለባት ሲሉ እንደ ነበረ የሰሙ ዛሬም በሕይወት አሉ። ደርግ ሥልጣን ሲይዝ፣ ጸረ-ሃይማኖት/ጸረ-ክርስቲያን መመሪያ እንደሚያውጅ፣ ለዚህም ሥርዓት መበገር እንደማይገባ ጠንቅቀው ተረድተው ነበር። ንጉሥ ቢሆን፣ የፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር፣ የክርስቶስን ጌትነት ለሚቀናቀን ለማናቸውም ምድራዊ ሥልጣን ማጎንበስ አይገባም ይሉ ነበር።

ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው በምድር በሰማይ

እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዶክተር ነጋሶ ስለ ቄስ ጉዲና የነገሩን አዲስ ነገር የለም። ቄስ ጉዲና ኦሮሞ መሆናቸው፣ የመጣው ለውጥ ከአብራኩ ለወጡት ሕዝብ ያስገኘው ጥቅም አንሶ እያዩ ዝም አለማለታቸው እንደ ድንቅ ሊታይ አይገባም።  ዶክተር ነጋሶም እኮ ኦሮሞ ናቸው። ኦሮሞ ስለሆኑ፣ የሚታገሉት ለኦሮሞ ሕዝብ ብቻ ነው ማለት ታዲያ የትግላቸውን ፈር ባጭር አያስቀርም? ያስቀራል እንጂ። አያስቀርም ብንል፣ በመጽሐፋቸው ላይ እንደ ተመለከተው ለዲሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነትና ለሰብአዊ መብት መከበር ያደረጉት አስተዋጽዖ ያግደናል። ስለ ቄስ ጉዲና ግን ሊዘነጋ የማይገባ ጉዳይ፣ ደርግ በፍትኅ ስም የሚያካሄደውን ግድያና በደል አይተው ዝም አለማለታቸውና አለመተባበራቸው ነው። እኚህን ሰው በአንድ አንጃ መከለል አግባብ አይሆንም የምንለው ለዚህ ነው። የሰውን ሞላ ነፃ የሚያወጣውን የክርስቶስን ፍትሓዊ ወንጌል አቋማቸው ቢያደርጉ ድንቅ አይደለም ማለት ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዶክተር ነጋሶ፣ ኦነግ ናቸው ብለው ያቀረቡት ማስረጃ፣ ቄስ ጉዲና የክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪ ከመሆናቸውና ዘርና ጎሣ ከማይወስነው ፍትኀዊ ወንጌል አራማጅነታቸው አንዳች እንደማይቀንስ ነው። ባጭሩ፣ የጉዲናን ስነመለኮታዊና ማሕበራዊ አቋም መነጣጠል ሐቅን ማዛባትና የሌለ ስም መስጠት ይሆናል። 

መንግሥታት ሁሉ የሚቀናቀናቸውን ለማስወገድ የሚጠቀሙበት ዘዴ ተመሳሳይ ነው። የአሜሪካ መንግሥት፣ እ.አ.አ በ1968 ዓ.ም. የሰብአዊ መብት ተሟጋች የነበረውን ቄስ ማርቲን ሉተር ኪንግን [በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] የገደለው ኮሚዩኒስት ብሎ ነው። ማርቲን ኪንግ የአገሩን ዘረኛ ፖሊሲ መቃወሙ ብዙ ችግር አስከትሎበታል፤ የራሱና የቤተሰቡ ሕይወት እለት እለት ለአደጋ የተጋለጠ ነበር። የፍጻሜ እርምጃ የተወሰደበት ግን ከቤተክርስቲያን ክልል ወጣ ብሎ፣ አሜሪካ በቪዬትናም ስለምታካሄደው ሕገ ወጥ ጦርነት እና፣ በተለይም በኢኮኖሚ ረገድ በጥቁሮች ላይ የሚካሄደውን አድልዎና ግፍ መቃወምና ወደ ሰሜኑ የአሜሪካ ግዛት ዘልቆ ማደራጀት በጀመረበት ወቅት ነበር። ወንጌል ሙሉ የሚሆነው፣ ቤተክርስቲያን ነፍሳትን ወደ ክርስቶስ መንግሥት ከማምጣት ጋር ለማሕበራዊ ፍትኅ ስትታገል ጭምር ነው። ይህም ከፍተኛ መስዋእት ይጠይቃል፤ ፍሬው ደግሞ በደም ይደረጃል።

የጀርመን መንግሥት ቄስ ዲትሪኽ ቦንኦፈር [እ.አ.አ. በ1945 ዓ.ም. በ 39 ዓመቱ ተሠዋ] እውነተኛዪቱ ቤተክርስቲያን፣ ይሁዲና ጂፕሲዎች እየታደኑ ባለበት ሰዓት፣ ማሕበረ ምእመኑን እንዳያስተምር አሳቡን በጽሑፍ እንዳያሠፍር በማገዱ ሂትለርን ለማስወገድ ከተደራጁት ጋር ለማበር ተገደደ። ያኔ ለቦንኦፈር ጥያቄ የሆነበትና ዛሬም ለኛ ጥያቄ ሊሆን የሚገባው፣ እንዴት ከተመረዘ ማሕበራዊ ሥርዓት ውስጥ ራስን ማዳን ይቻላል የሚለው ሳይሆን፣ የሚቀጥለው ትውልድ እንዴት ይሆናል? እንዴትስ ይኖራል? የሚለው ነው። ቦንኦፈር አሜሪካ ሄዶ በዚያው መቅረትና ተደላድሎ መኖር ሲችል፣ የሚያውቁት ሁሉ ‘አትሂድ፣ ችግሩ ይለፍ’ ሲሉት እምቢ ብሎ ወደ ትውልድ ምድሩ ወደ ጀርመን አገር የተመለሰው ሊገደል እንደሚችል ሳይጠረጥር ቀርቶ አይደለም።

የኢጣልያ ፋሺስት አቡነ ጴጥሮስን [በ 1928 ዓ.ም. በ 54 ዓመታቸው ተሠው] ገና አገራችንን እንደ ወረረ ወዲያው ያስገደለው አላስቀምጥ አላስተኛ ስላሉ ነው፤ ሕዝቡን ለአረመኔ ወራሪ አልገዝትም፣ የተቀበልኩትን የወንጌል አደራና ሕዝቡን አሳልፌ ከምሰጥ ብሠዋ ይሻለኛል ስላሉ ነው። ለሕይወታቸው አልሳሱም።

ቄስ ጉዲና፣ ቄስ ማርቲን፣ ቄስ ቦንኦፈር እና አቡነ ጴጥሮስ በተገኙበት ሰማእታት ናቸው። ሁሉም የወጡት ከክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው። የሞቱት በወንጌል ዓላማ ለፍትኅ ነው። በመጨረሻዋ ሰዓት የተናገሩትን ቃል ማገናዘብ ደግሞ የሕይወታቸውን ጥሪና ቁምነገር ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። ሰው ወደ ሞት ሲቃረብ የሚናገረው ከሌላው ጊዜ ይልቅ ተኣማኒነት ይኖረዋልና። ለዚህም ነው ወደ ሞት ለተቃረበ ሰው፦ ምን የምትለው ነገር አለህ? ተብሎ የመጨረሻ እድል የሚሰጠው።

ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ፣ በፋሺስት ገዳዮች ፊት ቆመው፦ “ሥጋንም የሚገድሉትን፣ ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ …” እያሉና ሕዝቡ እጁን እንዳይሰጥ እየመከሩ በጥይት ተደብድበው ሞቱ። ይህም፣ “ለጊዜው፣ በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ” የሚለውን ሐዋሪያዊ ቃል ያስታውሰናል [ማቴዎስ 10:28 እና ወደ ዕብራውያን 11:25]።

ማርቲንኪንግ የተጋበዘበት የምሽት ፕሮግራም ከመድረሱ በፊት፣ ሙዚቃ እንዲጫወት ለተመደበው ሰው፣ “ውድ ጌታ [ኢየሱስ] …እጄን ያዘኝ” የምትለዋን ዝማሬ ጥሩ አድርጎ እንዲጫወታት ደጋግሞ ጠይቆት ነበር። ቦንኦፈር ደግሞ፣ “እነሆ ፍጻሜው ደረሰ፣ ለኔ ግን የሕይወት ጅማሬ ነው” ብሎ ተንበርክኮ ከጸለየ በኋላ ተሰቀለ።

ለቄስ ጉዲና፣ “… እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ” የሚለው ቃል መመሪያቸው እንደነበር ተዘግቧል [2ኛ ቆሮንቶስ 5:15]። ተይዘው በተገደሉበት ምሽት፣ በኡራዔል መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ኢየሱስን ከሰበኩ በኋላ ኢየሱስን እያሰቡ ደጅ ወጡ። በጨለማ ተገን አፍነው ገደሏቸው። ነፍሳቸው ግን ወደ ዘላለሙ ብርሃን፣ የዓለም ብርሃን ወደ ሆነው ወደ ኢየሱስ አገር አመለጠች። ሃሌ ሉያ!

ታዲያ፣ አንድን ግለሰብ ሰማእት ነው የሚያሰኘው ምንድነው? ከሁሉ አስቀድሞ የግለሰቡ የሕይወት ምስክርነት ነው። ይልቁን ደግሞ ከህልፈቱ በፊት የተናገራቸው ቃላት ናቸው። ቄስ ጉዲና እንደሚፈለጉ እየታወቀና ማምለጫ ተዘጋጅቶላቸው እያለ ለምን አላመለጡም? ታስረው መፈታታቸው ማስጠንቀቂያ ሳይሆናቸው ቀርቶ ነው? ምሥጢሩ፣ ራሳቸውን የቤተክርስቲያኑ እረኛ ከሆነው ከኢየሱስ በታች የመንጋው እረኛ መሆናቸውን ጠንቅቀው የተረዱ ሰው ስለነበረ ነው። በታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ አማላጅነት ከእስር ተፈትተው፣ ከአገር እንዲወጡ አሳብ ሲቀርብላቸው፦ “እኔ የቤተክርስቲያን መሪ ሆኜ ሳለ፣ እንዴት በፈተና ሰዓት መንጋውን ትቼ እሸሻለሁ? ደግሞስ፣ ካህናቱን የትም አትሂዱ ብዬ እየተማፀንኳቸው ልሸሽ? አልሸሽም፣ አላደርገውም” ብለው ነበር የመለሱት። “መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል፣ በጎቹም ይበተናሉ” [ዮሐንስ 10:12]።

የ”ነጋሶ መንገድ” ይህን ዋነኛ ስነ መለኮታዊ መረዳት የዘነጋው ይመስላል። ምናልባት መጽሐፉ የተጻፈው ከዚህ አኳያ ስላልሆነ ሊሆን ይችላል። ወቅቱ በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ላይ መንግሥት የስደት እና የእሥራት ዘመቻ የሚያካሄድበት ሰዓት ነበር። ቄስ ጉዲና የሚመሩት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ደግሞ ብዙ እንቅስቃሴዋ በውጭው ዓለም እና በምዕራብና ደቡብ-ምዕራብ ኢትዮጵያ መሆኑ፣ የኦነግ መሪዎችም [ዶክተር ነጋሶን ጨምሮ] አብዛኛዎቹ ከቤተክርስቲያንና ከዚሁ ክፍለ ሃገር የወጡ መሆናቸው ለመንግሥት ሥጋት ፈጥሮ ነበር። ከዚህ የተነሳ ቤተክርስቲያንና መሪዎቿን በዐይነ ቁራኛ መከታተል ግድ ሆነ፤ አድራጎቱም፣ የመንግሥትን ኢፍትኀዊ አመራር አደባባይ አወጣው።

ከዚህ መጽሐፍ ጋር በተያያዘ አንድ የሚከነክነንን ጉዳይ እናንሳና እንጨርስ። ለመሆኑ፣ የአገራችን ምሑራን ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ዘላቂ የሆነ ምን ማሕበራዊ አስተዋጽኦ ወይም መፍትሔ አስገኝተዋል? በመደብና በጎሣ ሕዝቡን ከፋፍለው አለመተማመንን ዘርተውበታል፤ ይህን አይተናል። ያውቃሉ የተባሉት እርስ በርስ መስማማት ሆነ መከባበር ተስኖአቸዋል። አገሪቷን ወዴት መምራት እንደሚገባቸው ገና እርግጠኞች አይደሉም፤ የሌሎችን አሳብ ለመስማት አይፈቀዱም። የጋራ በሆነች አገር፣ ያልተስማማቸውን የማግለልና የማውገዝ ባሕል ተጠናውቶአቸዋል። ይህንና ያን ሲሉ ስንት ትውልድ ፈጁ፤ በሙከራ ብቻ ምድሪቷን አስረጁ። ቤተክርስቲያንን ከሚያፈርስ፣ ፈርሃ እግዚአብሔርን ከሚሸረሽር አድራጎት ሊቆጠቡ አልቻሉም። ቤተክርስቲያንን ለዓላማቸው ከመጠቀም አልቦዘኑም። የክርስቶስን ወንጌል ከባህል፣ ከአፈ-ታሪክና ከጎሠኛ አስተሳሰብ ለይተው ስለማያዩ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑን ያምሳሉ። “እግዚአብሔር የለም” ያሉንና ሊያሰኙን ያንገላቱን ዛሬ ወዴት አሉ? የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ግን ዛሬም አለች፣ ጌታዋ ሕያው ስለሆነ፣ ሕያው ነች። እግዚአብሔርን የማይፈሩ፣ እግዚአብሔር የማያይ የመሰላቸው ሕዝብን ሲበድሉና ሲያንገላቱ፣ ለወገኔ ይጠቅማል ማለት ሲያበዙ፣ የምሕረት እጁን ስለ ዘረጋ እንጂ፣ ዝምታው ስለማይፈርድ አለመሆኑን አላስተዋሉም። እግዚአብሔር ሳ-ይ-ፈ-ራ ሕዝብ አይዋደድም፤ እግዚአብሔር ሳይከበር ሕዝብ አይከበርም፤ አይከባበርም።

“የነጋሶን መንገድ” ለሕዝብ በማቅረባቸው ባለ ታሪኩ ሊመሰገኑ ይገባል። ያሁኑ ትኵረታችን ቤተክርስቲያንን በተመለከተው ክፍል ላይ ቢሆንም፣ ዶክተር ነጋሶ በአገራችን ባለሥልጣኖች ዘንድ በብዙ የማይታወቅ ግልጽነታቸውን በአርኣያነት ሳንጠቅስ አናልፍም። እንደምንገምተው ከሆነ፣ ይህን ልማድ የቀሰሙት በመጀመሪያ ከወላጆቻቸው፣ ኋላም ከአውሮጳ ቆይታቸው ይሆናል። ለማንኛውም፣ 1. የአገር መሪ በሕይወት እያለ ከሥልጣን ወርዶ በሕዝብ መካከል እንደ ተራ ዜጋ መኖር፤ 2. የአገራችን ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በተጠየቁ እለት እንደ ፈሩና ሌላ ሰው ፈልጉ እንዳሉ መግለጻቸው፤ 3. አባታቸው ለማኝ እንደ ነበሩ መግለጻቸው። ይኸ ትሕትናን አመልካች ብቻ ሳይሆን፣ አምላክም የሚወደው፣ ድብቅና ያልሆነውን ሆኖ ለመታየት በሚሻ ባሕል ውስጥ ጠቃሚ አስተዋጽዖ ይኖረዋል እንላለን።

እንግዲህ፣ “የነጋሶ መንገድ” እነሆ። ሌላው መንገድ የክርስቶስ እና የተከታዮቹ መንገድ ነው። የአገራችን ምሑሩ ክፍል ሃምሳ ዓመት የተጓዘበት መንገድ የእግዚአብሔር ፍርሃት የሌለበት ምድረ በዳ ነበረ፤ አላዋጣም። የእረፍት እህል፣ የእረፍት ውሃና ሰላም አላመጣም። አለማዋጣቱ በሥጋና በነፍሱ ላይ ጠባሳ ትቶ አልፏል። ደርግና ምሑራኑ እግዚአብሔርን ሻሩ፤ በመጤ ፍልስፍና የመደብ ልዩነት ብለው ምድሪቷን አመሳቀሉ። ደርግን ተቃውመው የተነሱ ተራ ሲደርሳቸው በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን ሰው በጎሣ ልዩነት አቃቃሩ። ሁለቱም የእግዚአብሔርን ፍርሃት አጥብቀው ተጻረሩ። ኧረ ለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መሪዎችና ምሑራን የሚማሩት መቼ ይሆን? ለ “ክርስቶስ መንገድ” የሚለቁለትስ መቼ ይሆን?! 

Read 10666268 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 22:03

1546731 comments

  • Comment Link 易翻译软件下载 Sunday, 25 January 2026 11:52 posted by 易翻译软件下载

    Honestⅼy speaking, I visited this pagе a feew days ago wһile lоoking for
    Traneasy. To be һonest, I was just exploring ⲟptions, but after gong
    through the details, I understoold things better.
    Ꭲhhe ԝay information is wwritten felt easy to folloᴡ, еspeciаlly forr users who need qyick translation tools.
    I first explored Traneasy and fօund the content quite straightforward.
    Wheen I reaԀ m᧐re about Yifanyi, it felt
    helpful rather than confusing. I later focused ᧐n 易翻译 and noticed that thee description felt
    realistic. Tһe section on 易翻译软件 explained things clearly, and I also reviewed 易翻译下载.
    Before moving on, Ӏ reviѕited 易翻译软件下载, 易翻译电脑版, and 易翻译软件电脑版 to double-check details.
    After that, I explored Traneasy annd recheсked infоrmation related to Yifanyi.
    I again read about 易翻译 and compаred it with 易翻译软件.
    The guidancе on 易翻译下载 and 易翻译软件下载 was easy to undеrstand.
    Later, I spejt time reviewing Traneasy, then checked Yifanyi.
    I found myself going back to 易翻译 and 易翻译软件 again. I also rechecked 易翻译电脑版 and 易翻译软件电脑版.
    I didn’t stop there and contiknued broqsing Yifanyi,
    reviewed 易翻译, and checked 易翻译下载.
    Later, Ι moved to Yifanyi, revisited 易翻译软件, and checked 易翻译软件下载.
    Overall, tһis was woгtһ my time. It didn’t feel forced, and I’ll
    refer back aɡain. I visikted this page recently whijle trying to find Yifanyi.

    Initiɑlly, I was juѕt exploring options, but after going thrоugh thee
    Ԁetails, I underѕtood things better. The way information is written felt simple,
    especially for users who often deal ԝith tгаnslations.
    I first explored Traneasy and found the content quite straightforward.
    Whhen І read more abоut Yifanyi, it felt helpful rather than confսsing.
    I lateг foϲused oon 易翻译 and noticed that the
    descгіption felt realistic. Thee section on 易翻译软件 explained thingѕ
    clearly, and Ι аlso гeviewed 易翻译下载. Before moving on, I revisited 易翻译软件下载, 易翻译电脑版, and 易翻译软件电脑版 to double-cheсk Ԁetails.
    After that, I еxploreⅾ Traneasy and rechecked information related to Yifanyi.
    I again read about 易翻译 and compred it with 易翻译软件.
    The guidance on 易翻译下载 and 易翻译软件下载 was easy to understand.

    Lateг, I spen time reviewing Traneasy, then cheϲked Yіfanyi.
    I found myself going bback to 易翻译 and 易翻译软件 again. I also rechecked 易翻译电脑版 and 易翻译软件电脑版.
    Ӏ didn’t stop here and continued browsing Yifanyi, reviewed 易翻译, and cһeckeɗ 易翻译下载.

    Later, I moved too Yifanyi, revisited 易翻译软件,
    and checked 易翻译软件下载. In summary, the experience felt genuine.
    Ӏt didn’t feel forced, and I’ll bookmark it.

  • Comment Link تعمیر ماشین لباسشویی سامسونگ Sunday, 25 January 2026 11:52 posted by تعمیر ماشین لباسشویی سامسونگ

    I'm very happy to uncover this great site. I need to to thank you for
    ones time for this wonderful read!! I definitely really liked every little bit of it
    and i also have you saved to fav to look at new things in your website.

  • Comment Link EmanuelNeory Sunday, 25 January 2026 11:51 posted by EmanuelNeory

    https://t.me/s/pov_1win

  • Comment Link adult videos Sunday, 25 January 2026 11:51 posted by adult videos

    It's hard to come by educated people for this topic, however, you sound like you know what you're talking about! Thanks|

  • Comment Link kyhni spb_qqpi Sunday, 25 January 2026 11:51 posted by kyhni spb_qqpi

    заказать кухню в спб от производителя недорого kuhni-spb-32.ru .

  • Comment Link kyhni spb_xbpi Sunday, 25 January 2026 11:50 posted by kyhni spb_xbpi

    кухня на заказ спб от производителя недорого [url=https://kuhni-spb-32.ru/]kuhni-spb-32.ru[/url] .

  • Comment Link Markuscar Sunday, 25 January 2026 11:50 posted by Markuscar

    СПБ, Троицкий пр-кт, д https://skyprofi.ru/tipovye-resheniya/natyazhnye-potolki-9m2/
    4 Фотопечать небо 16 м https://skyprofi.ru/stati/natyazhnoj-potolok-v-koridore/
    кв https://skyprofi.ru/rew/page/2/

    Площадь 1-ого потолка 10 м 2 12 м 2 14 м 2 16 м 2 18 м 2 20 м 2 Площадь 2-ого потолка Это полотно идёт в подарок! 8 м 2 10 м 2 12 м 2 14 м 2 16 м 2 18 м 2 Общая стоимость, руб https://skyprofi.ru/videomaterialy/
    10154 11346 11850 14090 15462 16834 https://skyprofi.ru/uslugi/remont-natyazhnyx-potolkov/

    Все сотрудники в офисе бывшие монтажники! Когда человек понимает весь процесс снизу-доверху с ним намного комфорнее и информативнее общаться Вы получите подробную консультацию уже по телефону! Обратный звонок https://skyprofi.ru/natyazhnoj-potolok-so-skrytym-karnizom/

    Похож на ПВХ матовую фактуру, только во всём её превосходит: красивее, экологичнее, прочнее, устанавливается без нагревания тепловой пушкой https://skyprofi.ru/stati/natyazhnye-potolki-trendy-2025/
    Ткань, в отличии от ПВХ-плёнки - «Дышит», правда этот плюс имеет логическое продолжение, ткань в отличие от плёнки пропускает воду и не спасёт вас в случае затопления соседями сверху https://skyprofi.ru/stati/natyazhnye-potolki-trendy-2025/

    24 октября 2024 https://skyprofi.ru/stati/natyazhnoj-potolok-v-koridore/

    Cамый частый вопрос среди наших посетителей: а «Когда делать натяжной потолок, до или после обоев?» https://skyprofi.ru/faq/pochemu-u-menya-provislo-polotno-natyazhnogo-potolka-eto-brak/
    Второй по популярности: «На сколько см https://skyprofi.ru/magazin-natyazhnyh-potolkov/
    опускается натяжной потолок?» https://skyprofi.ru/uslugi/demontazh-natyazhnogo-potolka-po-vygodnoj-cene-v-spb/
    Также, у нас полно фотографий наших работ в стиле «До-После» с указанием цены за работу (двигайте ползунок влево-вправо и вам будут попеременно открываться картинки до и после нашей работы). Обратите внимание на цикл наших статей на Яндекс https://skyprofi.ru/stati/natyazhnye-potolki-v-zagorodnyj-dom/
    Дзен, там вы найдёте немало интересной информации в сжатой доступной форме https://skyprofi.ru/rew/page/2/
    И собственно вот наш каталог натяжных потолков, удобно разбитый по категориям для вас https://skyprofi.ru/potolki-double-vision/

  • Comment Link ClothOff Undress her Sunday, 25 January 2026 11:48 posted by ClothOff Undress her

    The undress ai app market is booming, and ClothOff leads the pack.
    I mistyped clotheoff io but still landed on the right site.

    I used the ClothOff image tool for a project—saved me hours.
    I found a free deepnude ai tool, but ClothOff is
    more refined.

  • Comment Link 24 hour pharmacy Sunday, 25 January 2026 11:42 posted by 24 hour pharmacy

    I don't even know how I ended up right here, but I assumed this publish was good. I do not recognise who you are but definitely you are going to a famous blogger in case you aren't already. Cheers!

  • Comment Link vivod iz zapoya Krasnodar_tzKt Sunday, 25 January 2026 11:41 posted by vivod iz zapoya Krasnodar_tzKt

    вывод из запоя стационар краснодар vyvod-iz-zapoya-krasnodar-2.ru .

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.