×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:20

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ - ክፍል አንድ Featured

Rate this item
(0 votes)

የመጽሐፍ ግምገማ

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ - ክፍል አንድ

 

አቶ መርኪና በሰማንያ ሦስት ዓመታቸው በኅዳር ወር 2000 ዓ.ም. ወደ ጌታ ተሻግረዋል። በቀብራቸው ሥርዓት ላይ ከስምንት ሺህ በላይ ሰው እንደ ተገኘ ታውቋል። ይህ ክፍል “የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክና የወላይታ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ታሪክ” በሚል ግለሰቡ ጽፈው በ 2000 ዓ.ም. ከታተመው መጽሐፍ የተቀነጨበ ነው። ከዚህ ቀደም እንዳደረግነው ሁሉ መጽሐፉን ከመገምገም ይልቅ ከተለያዩ የመጽሐፉ ክፍሎች ቆንጽሎ በማስነበብ አንባቢዎቻችንን በጌታ ሥራ ማደፋፈር የተሻለ እንደ ሆነ ተገንዝበናል። ከ 13 ዓመት በፊት አቶ አማኑኤል አብርሃም “የሕይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ ካሳተሙት መጽሐፍ ጋር ተመሳሳይነት አለው። የሚያስገርመው ሁለቱም መሪዎች በቅርብ መተዋወቃቸው ነው፤ ለምሳሌ፣ መርኪና በ ገጽ 44 ላይ ስለ አማኑኤል ያሉትን እንመልከት፦

 

“አንድ ቀን የሚስዮኑ ኃላፊዎች፣ “በታንዛንያ ለሚካሄደው የሉተራን ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ስብሰባ የሲዳማን ቤተ ክርስቲያን ወክለህ እንድትገኝ ተጠርተሃል፣ ጉባኤው የሚካሄደው በክሊማንጃሮ ተራራ አጠገብ ነው” አሉኝ። እኔም ተደነቅሁና፣ “ከእነዚያ ታላላቅ ሰዎች ጋር ጉባኤውን ለመካፈል እኔ ምን ዕውቀትና ችሎታ አለኝ? የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ፣ ወደሚልከኝ ቦታ ሁሉ እሄዳለሁ” ብዬ “እሺ” አልኩኝ። ተነሥቼ የሚስዮኑ መሪዎች ጉባኤው ወደሚካሄድበት አገር ለመጓዝ ወደሚዘጋጅበት ወደ አዲስ አበባ ሄድኩኝ። ዶ/ር አማኑኤል አብርሃም እና ዶ/ር አማኑኤል ገ/ሥላሴ ከሚሄዱት መካከል ነበሩ። ለጉዞው ከመነሣታችን በፊት ዶ/ር አማኑኤል አብርሃም በመኖሪያ ቤታቸው የእራት ግብዣ አደረጉልን። በሕይወቴ እንደዚያ ዓይነት ግብዣ አይቼ አላውቅም። እሳቸው በጊዜው በኢትዮጵያ መንግሥት የተሾሙ ሚኒስትር ነበሩ። በድሆች መካከል ክርስቶስ ራሱን ዝቅ እንዳደረገ፣ እርሳቸው በእኛ መካከል ራሳቸውን ዝቅ ያደረጉ ነበሩ።”

 

ሁለቱም መጽሐፎች በድምሩ ቢያንስ የመቶ ዓመት የቤተክርስቲያንን ታሪክ ከነበረው ማሕበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ ይተረጉማሉ። ሁለቱም ጸሐፊዎች በሂደቶቹ ውስጥ ታዛቢ ብቻ ሳይሆኑ መሪዎችም ስለ ነበሩ ያቀረቡልንን ሠነድ ጠቃሚነት አጉልቶታል። በኛ አስተያየት ይህን መሰል መጽሐፎችን በቤተክርስቲያን አመራር ላይ የሚገኙ ሁሉ በጥንቃቄ ሊያነብቡ ይገባል። በመጽሐፍ ቅዱስ ትምሀርት ቤቶችና ሴሚናሪዎች እንደዚሁም የመሪነት ሥልጠና በሚሰጡባቸው ቦታዎች ሁሉ ዋነኛ የመማርያና የመወያያ መጽሐፎች ሆነው ሊቀርቡ ይገባል። የሁለቱን መሪዎች አመራር በጥንቃቄ መመርመር ተገቢም ጠቃሚም ነው። እነዚህን ዓይነት አገልጋዮች ስለ ሰጠን አምላካችንን በብዙ ልናመሰግነው ያስፈልጋል። በተጨማሪም አልተተረጎሙ እንደ ሆነ የአቶ አማኑኤል ወደ አማርኛ፣ የአቶ መርኪና ደግሞ ወደ እንግሊዝኛ ሊተረጎሙ ይገባል እንላለን። ጽሑፉን እንድናዳርስ ላስቻሉን ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳቸው። የመርኪ ታሪክ እነሆ፦

 

አቶ መርኪና መጃ ተወልደው ያደጉት በደቡባዊ ኢትዮጵያ በወላይታ ዞን ነው። የአቶ መርኪና አባት አቶ መጃ ማዴሮ በ 1888 ዓ.ም. ከአቶ ማዴሮ ሃናቆ እና ከወ/ሮ አሽሬ ዳኖሌ ተወለዱ። አቶ መጃ ነገሮችን ፈጥነው የመረዳት ችሎታ የነበራቸው አስተዋይ ሰው ስለ ነበሩ፣ ሰዎች ከቅርብና ከሩቅ እየመጡ የምክር አገልግሎትን ከእርሳቸው ያገኙ ነበር። መልካም ባሕርያቸውም በኅብረተሰቡ መካከል አክብሮትን እንዲያገኙ አድርጎአቸዋል።

 

አንድ ቀን አባቴ ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ብዙ ክፉ ሥራዎችን ይሠራ እንደ ነበር ነገረኝ፤ እኔም ክፉ ሥራ ሠርቼ እንደ ነበር ተገነዘብኩ። ወንጌል ወደ ማኅበረሰባችን ከመድረሱ በፊት በጨለማ ሕይወት ውስጥ እንኖር ስለ ነበረ፣ የተሻለው ነገር ምን እንደ ሆነ አናውቅም ነበረ። ከዚህም የተነሣ ሕይወታችን ጎስቋላና በፍርሃት የተሞላ ነበር። ከበሽታና ከሞት ለማምለጥ፣ አዝመራችን የበለጠ ምርት እንዲሰጠንና ሌላም ብዙ የሕይወት ውጣ ውረዶችን ለማለፍ መልካም መናፍስትንና ክፉ መናፍስትን መለማመን ነበረብን። ታላቅ እንደ መሆኔ መጠን፣ መሥዋዕት ለማቅረብ ከአባቴ ጋር የምሄደው እኔ ነበርኩ። በእኛ አካባቢ የታወቁ ሰዎች ወደ ፈለጉት አቅጣጫ አንድን ሰው አስከትለውና በቅሎ ላይ ተቀምጠው ይሄዱ ነበር። የአባቴን ካባ ተሸክሜ ከበቅሎአቸው ኋላ የምከተለው እኔ ነበርኩ። በእናቴ ቤተሰቦች በኩል አንድ ስሕተት ቢፈጸም ለመሥዋዕት የሚሆን በግ ይቀርባል። በአባቴ ቤተሰቦች በኩል ደግሞ ክፉ ሥራ ቢሠራ ወይፈን ይታረዳል። ከታረደው እንስሳ የተለያዩ ብልቶች ተወስደው ይጠበሱና ጠንቋዩ ይቀመጥ ባለበት ስፍራ ይቀመጣል። መስዋዕቱ ለሰይጣን የሚቀርብ ከሆነ ፍየል ይታረድና ሥጋው ጠንቋዩ ባዘዘበት ቦታ ይደረጋል። የበቆሎ እሸት እንደ ደረሰ ለዓመቱ ምስጋና የማቅረብ ሥርዓት ይካሄዳል። በቆሎውን ከነገለባው ጠብሶ ወይም ቀቅሎ በመንገድ ዳር ወይም ቤተሰብ ተሰብስቦ በሚያመልክበት ዛፍ ሥር ያኖሩታል። በተጨማሪም አባቴ ጣቶቹን በማር ውስጥ በማጥለቅና ወደ ሰማይ በመርጨት የጣዖት አምላክን ይለምን ነበር። የተረጨው ማር ተመልሶ ሲወድቅ ሮጬ ሄጄ ለመብላት እከጅላለሁ። ሆኖም አባቴ ያየኝ ይሆናል ብዬ እፈራ ስለ ነበር እተወዋለሁ።

 

በ1927 ዓ.ም. አንድ ቀን አባቴና እኔ ወደ ቤታችን ስንሄድ አረፋማውን ጅረት እየተከተልን ወደ ምንጩ አመራንና የአቶ አጌዶን ቤት ስናልፍ አቶ ዋንዳሮ ዳባሮ በአቶ አጌዶን ቤት ውስጥ ወንጌልን እየሰበኩ ኖሮ እኔና አባቴን አይተው ገብተን እንድንሰማ ጋበዙን። እኛም ተስማማን፣ ነገር ግን አባቴ እኔን በቅሎውን እንዳስር ሲያዝዘኝ ልጓሙን ፈትቼ እግሩን በገመድ በዛፍ ግንድ ላይ አሰርኩና ገብተን ለመስማት ተቀመጥን። አቶ ዋንዳሮ ስብከታቸውን ቀጠሉና በመካከሉም መዝሙር ጣልቃ እያስገቡ ያዘምሩ ነበር። ከመዝሙሮቹ አንዱ እንዲህ የሚል ነበር፦

     

በጎቹ የኢየሱስ ክርስቶስን ድምጽ ሲሰሙ

      ሊከተሉት ተፋጠኑ

      አስቀድመው ድምጹን ያልሰሙ ሊደርሱባቸው ተቻኮሉ

      እግዚአብሔርም ጠራቸውና ራሱን ገልጦላቸው ምሥጋናቸውን በደስታ ተቀበለ።

 

ሰባኪው ለረዥም ጊዜ ቢናገሩም እኔ የማስታውሰው ዋና ነጥብ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚች ዓለም አንድ ቀን ይመጣል የሚለውን ነበር። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። በእርሱ የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ይጥላቸዋል። “እናንተ ሰይጣንን ማምለክ አቁማችሁ በጌታ ኢየሱስ እመኑ። አለበለዚያ ግን ከሰይጣን ጋር ወደ እሳት ትጣላላችሁ። ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 201593 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:48

39716 comments

  • Comment Link zencortex where to buy Sunday, 28 April 2024 14:46 posted by zencortex where to buy

    Why people still make use of to read news papers when in this technological
    world all is accessible on net?

  • Comment Link Willieziday Sunday, 28 April 2024 14:42 posted by Willieziday

    Zet Casino No Deposit Bonus 2019

    Im Jahr 2019 hat das Zet Casino einen spannenden Bonus für alle neuen Spieler im Angebot. Der No Deposit Bonus ermöglicht es Spielern, ohne Einzahlung einen Bonus zu erhalten und direkt mit dem Spielen zu beginnen. Dies ist eine großartige Möglichkeit, um das Casino kennenzulernen und die verschiedenen Spiele auszuprobieren, ohne dabei eigenes Geld riskieren zu müssen.

    Um den No Deposit Bonus zu erhalten, müssen Spieler lediglich ein Konto im Zet Casino erstellen. Sobald das Konto eingerichtet ist, wird der Bonus automatisch gutgeschrieben und kann sofort genutzt werden. Dabei haben Spieler die Möglichkeit, verschiedene Spiele wie Spielautomaten, Tischspiele oder Live Casino Spiele zu spielen und echte Gewinne zu erzielen.

    Der No Deposit Bonus bietet eine großartige Gelegenheit, das Zet Casino risikofrei auszuprobieren und vielleicht sogar den ein oder anderen großen Gewinn zu erzielen. Spieler sollten jedoch darauf achten, dass sie die Bonusbedingungen und Umsatzanforderungen des Casinos beachten, um den Bonus in Echtgeld umwandeln zu können.

    Insgesamt bietet das Zet Casino mit seinem No Deposit Bonus für das Jahr 2019 eine großartige Möglichkeit, um sich mit dem Casino vertraut zu machen und die spannenden Spiele zu genießen. Spieler sollten diese Gelegenheit nutzen und sich den Bonus sichern, um ihre Gewinnchancen zu erhöhen und ein unterhaltsames Spielerlebnis zu erleben.
    https://zetcasino.one/

  • Comment Link Jamestrura Sunday, 28 April 2024 14:42 posted by Jamestrura

    Das Boomerang Casino Logo ist ein einzigartiges und auffälliges Design, das die Aufmerksamkeit der Spieler auf sich zieht. Das Logo besteht aus einem roten und weißen Boomerang, der sich dynamisch über einem blauen Hintergrund dreht.

    Das Casino-Logo spiegelt die Energie und Spannung wider, die die Spieler beim Spielen im Boomerang Casino erleben können. Der rote und weiße Farbton des Boomerangs symbolisiert auch Glück und Erfolg, was das Logo zu einem perfekten Symbol für ein Glücksspielunternehmen macht.

    Die geschwungene Form des Boomerangs im Logo verleiht ihm ein dynamisches und modernes Aussehen, das sich von anderen Casino-Logos abhebt. Dies macht das Boomerang Casino Logo leicht erkennbar und gut fГјr die Markenbildung.

    Das Logo des Boomerang Casinos trägt auch dazu bei, dass sich die Spieler mit der Marke identifizieren und eine starke Bindung zu dem Unternehmen aufbauen. Wenn Spieler das Logo sehen, werden sie sofort an das aufregende und unterhaltsame Spielerlebnis erinnert, das sie im Boomerang Casino genießen können.

    Insgesamt ist das Boomerang Casino Logo ein gelungenes Beispiel für ein kreatives und wirkungsvolles Design, das die Marke des Unternehmens effektiv repräsentiert und die Aufmerksamkeit der Spieler auf sich zieht. Es ist ein Symbol für Glück, Erfolg und Spaß – genau das, was man von einem erstklassigen Online-Casino erwarten kann.
    https://boomerangcasino.one/

  • Comment Link Hiramonery Sunday, 28 April 2024 14:42 posted by Hiramonery

    Tipico Casino Bonus Treue10

    Das Tipico Casino bietet seinen treuen Kunden einen besonderen Bonus an – den Treue10 Bonus. Dieser Bonus belohnt Spieler, die regelmäßig im Casino spielen und dem Anbieter treu bleiben. Doch was genau verbirgt sich hinter diesem Bonus und wie können Spieler davon profitieren?

    Der Treue10 Bonus ist ein exklusives Angebot für loyalen Spieler im Tipico Casino. Um diesen Bonus zu erhalten, müssen Spieler zunächst Mitglied im Treueprogramm des Casinos sein. Dies ist jedoch ganz einfach – Spieler können sich einfach anmelden und sofort von den Vorteilen des Treueprogramms profitieren.

    Sobald Spieler Mitglied im Treueprogramm sind, können sie sich für den Treue10 Bonus qualifizieren. Dieser Bonus wird den Spielern in Form von zusätzlichem Guthaben oder Freispielen gutgeschrieben. Spieler können dieses Bonusguthaben verwenden, um ihre Lieblingsspiele im Casino zu spielen und so ihre Gewinnchancen zu erhöhen.

    Der Treue10 Bonus ist eine tolle Möglichkeit für Spieler, noch mehr aus ihrem Spielerlebnis im Tipico Casino herauszuholen. Durch regelmäßiges Spielen und Treue zum Anbieter können Spieler sich zusätzliches Guthaben sichern und damit ihre Gewinnchancen steigern.

    Wenn auch Sie von den exklusiven Vorteilen des Treue10 Bonus profitieren möchten, sollten Sie sich noch heute im Tipico Casino anmelden und Mitglied im Treueprogramm werden. Mit etwas Glück und Geschick können auch Sie sich den begehrten Treue10 Bonus sichern und so noch mehr Spaß beim Spielen im Casino haben.
    https://tipicocasino.one/

  • Comment Link video porno Sunday, 28 April 2024 14:13 posted by video porno

    Fantastic beat ! I would like to apprentice while you amend your website, how can i subscribe for a blog web site? The account helped me a acceptable deal. I had been a little bit acquainted of this your broadcast offered bright clear idea

  • Comment Link Darrenwrarm Sunday, 28 April 2024 13:40 posted by Darrenwrarm

    address btc mixer

  • Comment Link vletmpog Sunday, 28 April 2024 13:14 posted by vletmpog

    У вас возникли проблемы психического характера? Артур Евгеньевич Спиглазов - врач-психиатр окажет вам лечение и психологическую помощь. Вы справитесь с тревогами и страхами, почувствуете вкус к жизни и обретете веру в себя. Требуется заключение о сделкоспособности? Jur24.ru - сайт, где есть возможность записаться на прием к врачу уже сегодня. Артур Евгеньевич - настоящий специалист своего дела. Профессионал подберет подходящие для вас препараты и поставит верный диагноз. С ним вы можете проконсультироваться при возникновении интересующих вопросов, касаемо лечения.

  • Comment Link phen q Sunday, 28 April 2024 12:47 posted by phen q

    I have read a few excellent stuff here. Definitely price bookmarking for revisiting.
    I surprise how a lot attempt you place to create this sort
    of magnificent informative web site.

  • Comment Link vo_ntorg_zyma Sunday, 28 April 2024 12:45 posted by vo_ntorg_zyma

    Воєнторг
    10. Лучшие бронежилеты и шлемы для защиты
    тактичні рюкзаки купити https://voentorgklyp.kiev.ua/ryukzaky-sumky/taktychni-ryukzaky/ .

  • Comment Link Papetc Sunday, 28 April 2024 11:58 posted by Papetc

    buy metoprolol no prescription - olmesartan 20mg over the counter oral adalat 10mg

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.