×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:28

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት። Featured

Rate this item
(0 votes)

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት።

በዚህ ክፍል በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መርኪና የጻፉትን በአጭር በአጭሩ በመጥቀስ እንጨርሳለን።

ዘርና ጎሣ። ጊዜው 1948 ሆኖ ከኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን ጋር እየሠራሁ በነበርኩበት ወቅት ታንዛንያ የተካሄደውን የሉተራን ዓለም ፌዴሬሽን ጉባዔ ለመካፈል አጋጣሚ አገኘሁ …በረርንና ኬንያ ደረስን … በሚቀጥለው ቀን ጧት በአውቶቡስ ተጓዝን …የአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች ሁለት አፍሪካውያን ነበሩ። በአውቶቡሱ ውስጥ አንድ እንግሊዛዊ ከነሚስቱ ተቀምጦ ነበር። ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ለራት ቆምንና ከእንግሊዛዊውና ከሚስቱ ጋር ወደ ምግብ ቤት አመራን። በልተን ስንወጣ ከአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች አንዱ፦ “እናንተ አፍሪካውያን ናችሁ። እዚህ ነጮች ብቻ እንዲገቡ በተፈቀደበት ቤት ለምን ገብታችሁ ትበላላችሁ” አለን። እኛም፣ “በአገራችን እንደዚህ ዓይነት ነገር የተከለከለ አይደለም” አልን። እኛ በዚህ አገር ፍጹም እንግዶች ነን። የኬንያ አሽከርካሪዎች የአዳም ልጆች አይደሉም? የውጪ ዜጎችስ የማን ዘር ናቸው? እንደዚህ ዓይነት የዘር መድልዎ ለእኛ እንግዳ ነገር ነበር። እንደዚህ ዓይነቱን ልዩነት እግዚአብሔር ያስወግድ ብለን ጸለይን። [ገጽ 45]

አሜሪካ በነበርንበት ጊዜ [1957] ዳግመኛ የጥቁርና የነጭ ልዩነት ተነሣ። ልጆቻቸው በተመሳሳይ ትምህርት ቤት አይማሩም፤ በጸሎት ቤት ውስጥ በአንድነት አይቀመጡም፤ በአንድ አውቶቡስም አብረው አይሳፈሩም። ይህ የእግዚአብሔርን ቃል የሚጻረርና ማንም የማይክደው ሃቅ ነው። በአሜሪካ በቆየሁበት ጊዜ የተመለከትኩት አንድ ደካማ ነጥብና በአዕምሮዬ ለተፈጠረብኝ ጥያቄ መልስ ያጣሁለት ቢኖር የቆዳ ልዩነት ጉዳይ ነበር። “ዓለማውያኖች ደስ የሚላቸውን ያድርጉ፤ ነገር ግን ክርስቲያኖች ለምን በጌታ ቃል ላይ አይቆሙም? “የክርስቶስን ፈለግ ለምን አይከተሉም? ክርስቶስ ራስ ሲሆን፣ እኛ ብልቶቹ ነን። ልዩነት የለም፤ የአሜሪካ ክርስቲያኖች ይህን ማሰብ ይኖርባቸዋል።” [ገጽ 91-92]

እኛ ክርስቶስን ስናምን በጎሣና በዘር ልዩነት ነበረን። የእግዚአብሔር ቃል በመጀመሪያ አዳምና ሔዋንን ፈጠራቸው፣ ከእነርሱ የሰዎች ዘር ሁሉ እንደ መጣ ቃሉ ይናገራል። ስለዚህ እኛ አማኞች ከሆንን በኋላ በፊት ከማናገኛቸው ሰዎች ጋር አብረን በላን፣ ጠጣን፤ አንድነት አደረግን። ስለዚህ በአሜሪካን አገር ያላችሁ አማኞች አሳባችሁን ለውጣችሁ ጥቁሮችን ብታስተምሩ ጥሩ ነው።” [ገጽ 176]

በአጋንንት ላይ ሥልጣን። ነባር ቤተክርስቲያን እያጠናከርን፣ ለአዳዲስ ቤተክርስቲያናት ቤት ለመሥራት የሚመች ቦታ እንመርጥ ነበር። በየሄድንበት ቦታ ቃሉን እንሰብካለን። ሾሻ ወደሚባለው አካባቢ ስንደርስ፣ በርኩስ መንፈስ የሚሠቃይ ሰው ነበር። ብዙውን ጊዜ ሰይጣን እሳት ውስጥ እንዲሁም ወንዝ እየወሰደውም ይጥለው ነበር። ጎረቤቶቹም በሰንሰለት ማሰሩ ሰልችቷቸው ነበር። በሰይጣን የተያዘው አቶ ሻለሞ የሚባለው ሰው ሲሆን፣ ከእኔ ጋር አቶ አንጁሎ የሚባል ወንጌላዊ ነበርና ሰውየውን አይቶት መጽሐፍ ቅዱስን በራሱ ላይ ጭነን እንጸልይለት፣ ሰይጣኑም ይለቅቀዋል አለኝ። ወደ እርሱ ስንጠጋ፣ ሰውየው እያለቀሰ ወደ ጓዳ ገብቶ ተደበቀ። እኛም ተከትለነው “በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከእርሱ ውጣ” ብለን ጸለይንና፣ ደግመንም፣ “ይህ የእግዚአብሔር ሰው ነው። በክርስቶስ ደምና በቃሉ እናዝሃለን፤ ለቅቀኸው ውጣ” አልን። መጽሐፍ ቅዱሱንም በላዩ ላይ ጭነን እንደገና ጸለይን። የሰይጣን መንፈስም ለቀቀውና ሰውየው ደህና ሆነ። ሦስት ዓመት ሙሉ በሰንሰለት ታስሮ የኖረ ሰው በጌታ ኃይል ፈውስን አገኘ። [ገጽ 57-58]

እምነት፣ ታማኝነትና መስዋእትነት። መባ አሰጣጣቸው ሁልጊዜ የሚያስደንቀኝ ነበር። በወቅቱ ገንዘብ ያልያዙ ሰዎች ቃል ሲገቡ ይመዘገባሉ። ገንዘብ ይዘው የመጡትም ወዲያው ይከፍላሉ። ባለፈው ዓመት ቃል ገብቶ የነበረ ሰው ገንዘቡን ሳይሰጥ ቢሞት ሚስቱ አምጥታ ትከፍላለች። ለምሳሌ፣ የአቶ ሳቃቶ ሚስት በሞተች ጊዜ ቃል ገብታ የነበረችውን ገንዘብ ባለቤቷ ከፍሏል። አማኞች ሥራቸው ገንዘብ ሰጥተው የወንጌላዊውን ወጪ ችለው መላክ ብቻ አይደለም። የለበሱትን ልብስ አውልቀው ለጌታ አገልጋዮች እንዲሰጥላቸው ያበረክቱ ነበር። ሰዓታቸውንም ከእጃቸው እያወለቁ ይሰጡ ነበር። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ጫማቸውን እያወለቁ ይሰጡ ነበር። በሬ፣ ላምና በቅሎ የሚሰጡም ነበሩ። ልጆች ደግሞ ያረቡትን ዶሮ ይሰጡ ነበር። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ብዙዎች ወንጌላዊ ሆነው ለማገልገል ራሳቸውን ይሰጡ ነበር። ይህን የሚያደርጉት ለጌታ ካላቸው ፍቅር የተነሣ እንጂ ማንም አስገድዷቸው አልነበረም …አቶ ኤካሶም “እኔም አንድ ላም አለችኝ። የላሟን ወተት ግማሽ ለጌታ መስጠት እፈልጋለሁ” አለ። በሚቀጥለው ቀንም ለሁለተኛ ጊዜ ቆሞ፣ “እኔ የላሟን ወተት ከጌታ ጋር መካፈል አልፈልግም። ላሟን እንዳለች ለጌታ ሰጥቻለሁ” አለ …በስብሰባው መጨረሻ ቀን አሁንም አቶ ኤካሶ ተነሥቶ፣ “የወላይታ ቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ቦርድ አባል ከምሆን፣ ወንጌላዊ ሆኜ ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። ጌታ ወደ ላከኝ ቦታ ሁሉ እየሄድኩ ማገልገል የተሻለ ነው። ወንጌላዊ ሆኜ በሕይወቴ ሙሉ ጌታን ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። [ገጽ 59-60፣ 82]  

ገንዘብና አገልግሎት። ወደ ዳሞት ፍላሳ ማኅበር ኮርስ ለመጀመር በምንሄድበት ጊዜ ከአቶ አታሎ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው፣ “የት ትሄዳላችሁ?” ብሎ ጠየቀን። እኛም “ኮርስ ልናስተምር ነው የመጣነው” ብለን መለስን። ሰውዬውም፣ “በሶዶ ዓመታዊ ጉባዔ የሰጠነው ገንዘብ ተልኳል። አሁን ወደ እኛ መንደር ብትመጡ፣ ሌላ ገንዘብ ዳግመኛ የሚሰጣችሁ የለም” አለን። እኛም መልሰን “እኛ ገንዘብ ለመጠየቅ አልመጣንም፣ የመጣነው የእግዚአብሔርን ቃል ልናስተምር ነው፤ አንተም መጥተህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ” አልነው …ስብሰባው ለሦስት ቀን ቀጠለ። አንዲት እኔ የማላውቃት ሴት ሁልጊዜም ስብሰባ ላይ የምትገኝ ስትሆን፣ ከፊት ለፊት ተቀምጣለች። እርሷም በወገቧ ያለውን መቀነቷን ፈታችና ገንዘብ አውጥታ ሰጠች። ቀጥላም የአንገት ልብሷን/ነጠላዋን፣ በቀጣዩም ጊዜ ሻሽዋን ሰጠች። በመጨረሻም፣ የፈረስ መጋለቢያ ሱሪዋን ሰጠች። “ገንዘብ የሚሰጥ የለም” ይል የነበረው ሰው በየቀኑ በበቅሎው ላይ እየተቀመጠ ይመጣና ስብሰባውን ይካፈል ነበር። በቅሎውንም ከደጅ ሣር በሚበላበት ቦታ ያስረዋል። በኮርሱ መጨረሻ ቀን ተነሥቶ ቆመና “አስቀድሜ የምትሰበሰቡት ገንዘብ ለመውሰድ ነው። ማንም ግን የሚሰጣቸው የለም ብዬ ነበር። አሁን የእግዚአብሔር መንፈስ በቅሎዬን እንድሰጥ አሳስቦኛል። ከጌታ መንፈስ ጋር መከራከር አልችልምና በቅሎዬን ሰጥቻለሁ” አለና አምጥቶ ሰጠ። እኛም ጌታን አመሰግን።[ገጽ 79-80]

የሴቶች ጉዳይ። ሴቶች ቸል ይባላሉ ወይ? በቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ክትትል ሚስ በርግስተን ከወላይታ ወረዳ አብያተ ክርስቲያናት ልጃገረዶችን መርጠው መጽሐፍ ቅዱስና እጅ ሥራ ብዙውን ጊዜ ሹራብ ሥራ እንዲማሩ ተደረገ። ሴቶች ወገባቸውን የሚያስሩበትንና ለልጆቻቸውም ደግሞ ሹራብ ይሠራሉ። ሥልጠና አግኝተው የሚሄዱ ልጃገረዶች በተራቸው ሄደው በቤተክርስቲያን የሚገኙትን ሴቶች መጽሐፍ ቅዱስንና የሹራብ ሥራን ያስተምራሉ። [ገጽ 68]

ቤተክርስቲያንና መንግሥት። በ1953 ዓ.ም. አንድ ጊዜ በአካባቢያችን የብዙ ሕዝብ መታሠር ነበር። ክርስቲያኖቹም መልሰው፣ “መንግሥት ሃይማኖት የግል አገር የጋራ መሆኑን በሕገ መንግሥቱ ደንግጓል። እንዴት እንደ ከብት እየነዳችሁን በእስር ቤት ታጉሩናላችሁ?” አሉ …[አዲስ አበባ ሄደን] ማመልከቻ ለማቅረብ ወሰንን። የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘን ከስድስት ኪሎ ወደ ታላቁ ቤተመንግሥት አመራን። ሁላችንም አቤት እያልን እንጮህና እናለቅስ ነበር። ንጉሡም ጩኸታችንንና ለቅሶአችንን ሰምተው ወደ እርሳቸው እንዲያቀርቡን ወታደሮቻቸውን አዘዙ። [ገጽ 132]

ቤተክርስቲያንና ልማት። የወንጌል ሥራና የዕድገት/የልማት ሥራ ጎን ለጎን የሚሄዱ ናቸው። በአውራጃችን ውስጥ መሃይምነትን ለማጥፋት 738 ቤተክርስቲያናት ትምህርት ቤቶችን አዘጋጅተው አስተምረዋል። ዶክተሮች፣ አስተዳዳሪዎች፣ አስተማሪዎች፣ የሕግ ባለ ሙያዎች እና ሌሎች በርካታ ምሁራን ከእነዚያ ቤተክርስቲያን መሥርታ ካስተማረቻቸው ትምህርት ቤቶች የፈለቁ ናቸው። ለወላይታ በዘመናዊ ትምህርት መራመድ በሩን የከፈተችው ቤተክርስቲያን ነች። [ገጽ 123]                              ተፈጸመ።

 

�� ���P�y p ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 1962445 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:46

583802 comments

  • Comment Link tt88.zi Monday, 08 December 2025 08:57 posted by tt88.zi

    Các trò chơi trên web đa dạng và phong phú.

  • Comment Link pg88sr.com Monday, 08 December 2025 08:52 posted by pg88sr.com

    Giao diện web đơn giản nhưng tinh tế và trực quan.

  • Comment Link augenlidstraffung frankfurt Monday, 08 December 2025 08:42 posted by augenlidstraffung frankfurt

    Hello, i think that i saw you visited my blog so i came to “return the favor”.I'm attempting to find things to enhance my web site!I suppose its ok to use a few
    of your ideas!!

  • Comment Link SKYSHOT crackers online Monday, 08 December 2025 08:38 posted by SKYSHOT crackers online

    Lookіng for the beѕt plɑce tо explore premium crackers online?
    Thousands օf customers rely ߋn SKYSHOT crackers online еvery festive season. People ԝhߋ look forr authentic brands οften choose online sellers tһat directly
    sourcfe from Sivakasi manufacturers. Special festival combos ɑnd exclusive items arre easily ɑvailable оn SKYSHOT crackers online.
    Ꮃith proper categories аnd filters, users ⅽan quicklʏ discover
    exactly ᴡhat they need. During peak festice m᧐nths, trusted sellers like SKYSHOT crackers online mаke suгe supplies are alwаys ready.
    Sⲟ if you are planning yourr next celebration,
    chdck trusted stores аnd enjoy a hassle-free shopping experience.

  • Comment Link Contributor-929946 Monday, 08 December 2025 08:35 posted by Contributor-929946

    Сообщайте прежде, чем действовать: Успех Манифестора зависит от того, насколько они могут проявлять инициативу, не вызывая сопротивления. Что такое Дизайн Человека, и как он может быть вам полезен. Профессиональная независимость. Как Дизайн Человека помогает в жизни? Дизайн человека не предсказывает будущее, а помогает описать уникальную природу каждого человека. Как сделать правильный выбор на работе, в любви и в жизни. Какой самый редкий тип в дизайне человека?
    https://ncb-human-design-gjs-ru-iva.hdea.ru

  • Comment Link J8 Monday, 08 December 2025 08:31 posted by J8

    Sitemap guide to navigate J8VIP features effortlessly

  • Comment Link additional maths tuition for o level singapore Monday, 08 December 2025 08:30 posted by additional maths tuition for o level singapore

    In the Singapore system, secondary school math tuition plays а vital role
    in fostering discipline іn math studies.


    Lah lor, Singapore students аlways ϲome fіrst in global math sia!





    For parents, motivate reflection іn Singapore math tuition'ѕ practice.
    Secondary math tuition journals promote. Тhrough secondary 1 math tuition, operations ѕet.





    The philanthropic aspect ߋf some secondary 2 math tuition programs ⲣrovides scholarships.
    Secondary 2 math tuition һelp underprivileged trainees.
    Generous secondary 2 math tuition promotes equity. Secondary 2
    math tuition returns tо society.



    Іn secondary 3, math exams test advanced subjects tһat foгm thе foundation օf O-Level preparation, mаking high scores essential fⲟr constructing momentum tߋward tһе final yeaг.
    Ɗoing weⅼl avoids understanding spaces thаt couⅼd prevent performance іn thе Ⲟ-Levels,
    where math grades heavily influence general L1R5 scores. Tһіs accomplishment not
    juѕt increases confidence hoԝeveг also enhances eligibility for junior college ߋr
    polytechnic programs.



    Secondary 4 exams promote deplth іn Singapore'ѕ structure.

    Secondary 4 math tuition questions fundamentals. Ƭhis provocation improves O-Level gratitude.
    Secondary 4 math tuition believes deeply.



    Math ցoes further than exam preparation; it'ѕ an indispensable competency
    іn thе AӀ erɑ, essential for developing ethical аnd efficient AІ solutions.




    Excelling аt math requіres fostering a love for the discipline ᴡhile applying its core ideas to everyday situations.



    Оne key aspect is that it helps in appreciating the interdisciplinary ⅼinks in math fгom
    diffеrent Singapore secondary papers.


    Online math tuition e-learning in Singapore boosts гesults
    Ƅy integrating parental involvement tools ⅼike shared dashboards.



    Ⴝia sia, don't bе anxious leh, secondary school ցot fun events, let уour child enjoy ԝithout stress.



    OMT's encouraging comments loopholes motivate development ѡay
    of thinking, aiding trainees love math ɑnd rеally feel inspired for examinations.




    Experience vedsatile knowing anytime, ɑnywhere tһrough OMT's
    comprehensive online е-learning platform, featuring limitless access tо video lessons and interactive tests.





    The holistic Singapore Math technique, ѡhich constructs
    multilayered analytical capabilities, underscores ԝhy math tuition іs indispensable fⲟr mastering thе cudriculum
    ɑnd preparing for future careers.



    Ϝօr PSLE success, tuition providеs tailored guidance tо weak areaѕ, like ratio and percentage issues, preventing typical risks tһroughout tһe examination.



    In Singapore's competitive education and learning landscape, secondary
    math tuition оffers the additional ѕide required t᧐ stand oᥙt in O Level rankings.





    Junior college math tuition іs critical fοr A Degrees as
    it strengthens understanding օf advanced calculus subjects ⅼike combination techniques
    and differential equations, ԝhich are central to the examination curriculum.




    OMT sets іtself ɑрart ԝith a proprietary curriculum tһat expands MOE
    c᧐ntent by including enrichment tasks targeted аt developing
    mathematical intuition.



    Individualized development tracking іn OMT'ѕ system reveals youг vulnerable pointѕ sia,
    enabling targeted practice fоr quality renovation.



    Math tuition inspires confidence tһrough success in lіttle
    landmarks, driving Singapore students tоward general exam triumphs.

  • Comment Link live wetten Strategie Monday, 08 December 2025 08:30 posted by live wetten Strategie

    kombiwette pferderennen

  • Comment Link chrome浏览器 Monday, 08 December 2025 08:15 posted by chrome浏览器

    The flow of the article made it easy to follow. Each section felt connected to the next, and the transitions were smooth and well thought out.

  • Comment Link آموزش شرط‌بندی آنلاین Monday, 08 December 2025 08:14 posted by آموزش شرط‌بندی آنلاین

    You look fresher than a $15 salad. Your vibrant energy and radiant appearance are truly remarkable. Like a gourmet salad bursting with crisp, colorful ingredients, you exude health, vitality, and zest for life. Your presence is refreshing and invigorating, brightening up any room you enter.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.