×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:28

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት። Featured

Rate this item
(0 votes)

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት።

በዚህ ክፍል በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መርኪና የጻፉትን በአጭር በአጭሩ በመጥቀስ እንጨርሳለን።

ዘርና ጎሣ። ጊዜው 1948 ሆኖ ከኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን ጋር እየሠራሁ በነበርኩበት ወቅት ታንዛንያ የተካሄደውን የሉተራን ዓለም ፌዴሬሽን ጉባዔ ለመካፈል አጋጣሚ አገኘሁ …በረርንና ኬንያ ደረስን … በሚቀጥለው ቀን ጧት በአውቶቡስ ተጓዝን …የአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች ሁለት አፍሪካውያን ነበሩ። በአውቶቡሱ ውስጥ አንድ እንግሊዛዊ ከነሚስቱ ተቀምጦ ነበር። ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ለራት ቆምንና ከእንግሊዛዊውና ከሚስቱ ጋር ወደ ምግብ ቤት አመራን። በልተን ስንወጣ ከአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች አንዱ፦ “እናንተ አፍሪካውያን ናችሁ። እዚህ ነጮች ብቻ እንዲገቡ በተፈቀደበት ቤት ለምን ገብታችሁ ትበላላችሁ” አለን። እኛም፣ “በአገራችን እንደዚህ ዓይነት ነገር የተከለከለ አይደለም” አልን። እኛ በዚህ አገር ፍጹም እንግዶች ነን። የኬንያ አሽከርካሪዎች የአዳም ልጆች አይደሉም? የውጪ ዜጎችስ የማን ዘር ናቸው? እንደዚህ ዓይነት የዘር መድልዎ ለእኛ እንግዳ ነገር ነበር። እንደዚህ ዓይነቱን ልዩነት እግዚአብሔር ያስወግድ ብለን ጸለይን። [ገጽ 45]

አሜሪካ በነበርንበት ጊዜ [1957] ዳግመኛ የጥቁርና የነጭ ልዩነት ተነሣ። ልጆቻቸው በተመሳሳይ ትምህርት ቤት አይማሩም፤ በጸሎት ቤት ውስጥ በአንድነት አይቀመጡም፤ በአንድ አውቶቡስም አብረው አይሳፈሩም። ይህ የእግዚአብሔርን ቃል የሚጻረርና ማንም የማይክደው ሃቅ ነው። በአሜሪካ በቆየሁበት ጊዜ የተመለከትኩት አንድ ደካማ ነጥብና በአዕምሮዬ ለተፈጠረብኝ ጥያቄ መልስ ያጣሁለት ቢኖር የቆዳ ልዩነት ጉዳይ ነበር። “ዓለማውያኖች ደስ የሚላቸውን ያድርጉ፤ ነገር ግን ክርስቲያኖች ለምን በጌታ ቃል ላይ አይቆሙም? “የክርስቶስን ፈለግ ለምን አይከተሉም? ክርስቶስ ራስ ሲሆን፣ እኛ ብልቶቹ ነን። ልዩነት የለም፤ የአሜሪካ ክርስቲያኖች ይህን ማሰብ ይኖርባቸዋል።” [ገጽ 91-92]

እኛ ክርስቶስን ስናምን በጎሣና በዘር ልዩነት ነበረን። የእግዚአብሔር ቃል በመጀመሪያ አዳምና ሔዋንን ፈጠራቸው፣ ከእነርሱ የሰዎች ዘር ሁሉ እንደ መጣ ቃሉ ይናገራል። ስለዚህ እኛ አማኞች ከሆንን በኋላ በፊት ከማናገኛቸው ሰዎች ጋር አብረን በላን፣ ጠጣን፤ አንድነት አደረግን። ስለዚህ በአሜሪካን አገር ያላችሁ አማኞች አሳባችሁን ለውጣችሁ ጥቁሮችን ብታስተምሩ ጥሩ ነው።” [ገጽ 176]

በአጋንንት ላይ ሥልጣን። ነባር ቤተክርስቲያን እያጠናከርን፣ ለአዳዲስ ቤተክርስቲያናት ቤት ለመሥራት የሚመች ቦታ እንመርጥ ነበር። በየሄድንበት ቦታ ቃሉን እንሰብካለን። ሾሻ ወደሚባለው አካባቢ ስንደርስ፣ በርኩስ መንፈስ የሚሠቃይ ሰው ነበር። ብዙውን ጊዜ ሰይጣን እሳት ውስጥ እንዲሁም ወንዝ እየወሰደውም ይጥለው ነበር። ጎረቤቶቹም በሰንሰለት ማሰሩ ሰልችቷቸው ነበር። በሰይጣን የተያዘው አቶ ሻለሞ የሚባለው ሰው ሲሆን፣ ከእኔ ጋር አቶ አንጁሎ የሚባል ወንጌላዊ ነበርና ሰውየውን አይቶት መጽሐፍ ቅዱስን በራሱ ላይ ጭነን እንጸልይለት፣ ሰይጣኑም ይለቅቀዋል አለኝ። ወደ እርሱ ስንጠጋ፣ ሰውየው እያለቀሰ ወደ ጓዳ ገብቶ ተደበቀ። እኛም ተከትለነው “በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከእርሱ ውጣ” ብለን ጸለይንና፣ ደግመንም፣ “ይህ የእግዚአብሔር ሰው ነው። በክርስቶስ ደምና በቃሉ እናዝሃለን፤ ለቅቀኸው ውጣ” አልን። መጽሐፍ ቅዱሱንም በላዩ ላይ ጭነን እንደገና ጸለይን። የሰይጣን መንፈስም ለቀቀውና ሰውየው ደህና ሆነ። ሦስት ዓመት ሙሉ በሰንሰለት ታስሮ የኖረ ሰው በጌታ ኃይል ፈውስን አገኘ። [ገጽ 57-58]

እምነት፣ ታማኝነትና መስዋእትነት። መባ አሰጣጣቸው ሁልጊዜ የሚያስደንቀኝ ነበር። በወቅቱ ገንዘብ ያልያዙ ሰዎች ቃል ሲገቡ ይመዘገባሉ። ገንዘብ ይዘው የመጡትም ወዲያው ይከፍላሉ። ባለፈው ዓመት ቃል ገብቶ የነበረ ሰው ገንዘቡን ሳይሰጥ ቢሞት ሚስቱ አምጥታ ትከፍላለች። ለምሳሌ፣ የአቶ ሳቃቶ ሚስት በሞተች ጊዜ ቃል ገብታ የነበረችውን ገንዘብ ባለቤቷ ከፍሏል። አማኞች ሥራቸው ገንዘብ ሰጥተው የወንጌላዊውን ወጪ ችለው መላክ ብቻ አይደለም። የለበሱትን ልብስ አውልቀው ለጌታ አገልጋዮች እንዲሰጥላቸው ያበረክቱ ነበር። ሰዓታቸውንም ከእጃቸው እያወለቁ ይሰጡ ነበር። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ጫማቸውን እያወለቁ ይሰጡ ነበር። በሬ፣ ላምና በቅሎ የሚሰጡም ነበሩ። ልጆች ደግሞ ያረቡትን ዶሮ ይሰጡ ነበር። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ብዙዎች ወንጌላዊ ሆነው ለማገልገል ራሳቸውን ይሰጡ ነበር። ይህን የሚያደርጉት ለጌታ ካላቸው ፍቅር የተነሣ እንጂ ማንም አስገድዷቸው አልነበረም …አቶ ኤካሶም “እኔም አንድ ላም አለችኝ። የላሟን ወተት ግማሽ ለጌታ መስጠት እፈልጋለሁ” አለ። በሚቀጥለው ቀንም ለሁለተኛ ጊዜ ቆሞ፣ “እኔ የላሟን ወተት ከጌታ ጋር መካፈል አልፈልግም። ላሟን እንዳለች ለጌታ ሰጥቻለሁ” አለ …በስብሰባው መጨረሻ ቀን አሁንም አቶ ኤካሶ ተነሥቶ፣ “የወላይታ ቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ቦርድ አባል ከምሆን፣ ወንጌላዊ ሆኜ ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። ጌታ ወደ ላከኝ ቦታ ሁሉ እየሄድኩ ማገልገል የተሻለ ነው። ወንጌላዊ ሆኜ በሕይወቴ ሙሉ ጌታን ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። [ገጽ 59-60፣ 82]  

ገንዘብና አገልግሎት። ወደ ዳሞት ፍላሳ ማኅበር ኮርስ ለመጀመር በምንሄድበት ጊዜ ከአቶ አታሎ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው፣ “የት ትሄዳላችሁ?” ብሎ ጠየቀን። እኛም “ኮርስ ልናስተምር ነው የመጣነው” ብለን መለስን። ሰውዬውም፣ “በሶዶ ዓመታዊ ጉባዔ የሰጠነው ገንዘብ ተልኳል። አሁን ወደ እኛ መንደር ብትመጡ፣ ሌላ ገንዘብ ዳግመኛ የሚሰጣችሁ የለም” አለን። እኛም መልሰን “እኛ ገንዘብ ለመጠየቅ አልመጣንም፣ የመጣነው የእግዚአብሔርን ቃል ልናስተምር ነው፤ አንተም መጥተህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ” አልነው …ስብሰባው ለሦስት ቀን ቀጠለ። አንዲት እኔ የማላውቃት ሴት ሁልጊዜም ስብሰባ ላይ የምትገኝ ስትሆን፣ ከፊት ለፊት ተቀምጣለች። እርሷም በወገቧ ያለውን መቀነቷን ፈታችና ገንዘብ አውጥታ ሰጠች። ቀጥላም የአንገት ልብሷን/ነጠላዋን፣ በቀጣዩም ጊዜ ሻሽዋን ሰጠች። በመጨረሻም፣ የፈረስ መጋለቢያ ሱሪዋን ሰጠች። “ገንዘብ የሚሰጥ የለም” ይል የነበረው ሰው በየቀኑ በበቅሎው ላይ እየተቀመጠ ይመጣና ስብሰባውን ይካፈል ነበር። በቅሎውንም ከደጅ ሣር በሚበላበት ቦታ ያስረዋል። በኮርሱ መጨረሻ ቀን ተነሥቶ ቆመና “አስቀድሜ የምትሰበሰቡት ገንዘብ ለመውሰድ ነው። ማንም ግን የሚሰጣቸው የለም ብዬ ነበር። አሁን የእግዚአብሔር መንፈስ በቅሎዬን እንድሰጥ አሳስቦኛል። ከጌታ መንፈስ ጋር መከራከር አልችልምና በቅሎዬን ሰጥቻለሁ” አለና አምጥቶ ሰጠ። እኛም ጌታን አመሰግን።[ገጽ 79-80]

የሴቶች ጉዳይ። ሴቶች ቸል ይባላሉ ወይ? በቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ክትትል ሚስ በርግስተን ከወላይታ ወረዳ አብያተ ክርስቲያናት ልጃገረዶችን መርጠው መጽሐፍ ቅዱስና እጅ ሥራ ብዙውን ጊዜ ሹራብ ሥራ እንዲማሩ ተደረገ። ሴቶች ወገባቸውን የሚያስሩበትንና ለልጆቻቸውም ደግሞ ሹራብ ይሠራሉ። ሥልጠና አግኝተው የሚሄዱ ልጃገረዶች በተራቸው ሄደው በቤተክርስቲያን የሚገኙትን ሴቶች መጽሐፍ ቅዱስንና የሹራብ ሥራን ያስተምራሉ። [ገጽ 68]

ቤተክርስቲያንና መንግሥት። በ1953 ዓ.ም. አንድ ጊዜ በአካባቢያችን የብዙ ሕዝብ መታሠር ነበር። ክርስቲያኖቹም መልሰው፣ “መንግሥት ሃይማኖት የግል አገር የጋራ መሆኑን በሕገ መንግሥቱ ደንግጓል። እንዴት እንደ ከብት እየነዳችሁን በእስር ቤት ታጉሩናላችሁ?” አሉ …[አዲስ አበባ ሄደን] ማመልከቻ ለማቅረብ ወሰንን። የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘን ከስድስት ኪሎ ወደ ታላቁ ቤተመንግሥት አመራን። ሁላችንም አቤት እያልን እንጮህና እናለቅስ ነበር። ንጉሡም ጩኸታችንንና ለቅሶአችንን ሰምተው ወደ እርሳቸው እንዲያቀርቡን ወታደሮቻቸውን አዘዙ። [ገጽ 132]

ቤተክርስቲያንና ልማት። የወንጌል ሥራና የዕድገት/የልማት ሥራ ጎን ለጎን የሚሄዱ ናቸው። በአውራጃችን ውስጥ መሃይምነትን ለማጥፋት 738 ቤተክርስቲያናት ትምህርት ቤቶችን አዘጋጅተው አስተምረዋል። ዶክተሮች፣ አስተዳዳሪዎች፣ አስተማሪዎች፣ የሕግ ባለ ሙያዎች እና ሌሎች በርካታ ምሁራን ከእነዚያ ቤተክርስቲያን መሥርታ ካስተማረቻቸው ትምህርት ቤቶች የፈለቁ ናቸው። ለወላይታ በዘመናዊ ትምህርት መራመድ በሩን የከፈተችው ቤተክርስቲያን ነች። [ገጽ 123]                              ተፈጸመ።

 

�� ���P�y p ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 1738024 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:46

505988 comments

  • Comment Link pawswap Thursday, 09 October 2025 10:02 posted by pawswap

    The using the API process is simple and the useful analytics makes it even better.

  • Comment Link find out here now Thursday, 09 October 2025 09:52 posted by find out here now

    Great goods from you, man. I've understand your stuff previous to and
    you're just extremely fantastic. I really like what you have acquired here, really like
    what you are stating and the way in which you say it. You make it enjoyable and you still care for
    to keep it wise. I can't wait to read far more from
    you. This is really a tremendous web site.

  • Comment Link LPVO scope Thursday, 09 October 2025 09:36 posted by LPVO scope

    在挑選合適的光學產品時,我最近發現rifle scope系列非常出色。對於喜歡戶外活動和打獵的朋友來說,huntingscope能夠提供清晰的視野與穩定的性能。如果是戰術用途,tactical scope以及LPVO
    scope都是不錯的選擇,而比賽用戶則會青睞competition rifle scope和ⅼong range rifle scope。對於專注於高精度需求的玩家,precision rifle scope與fіrst
    focal plane scope、ѕecond focal plane scope都能滿足不同情境的應用。網站還推薦precision hunting scope,讓獵人能夠在各種環境下保持最佳表現。更值得一提的是,budget rifle scope系列價格親民,卻依舊具備優秀品質,堪稱Ьest rifle scope選擇之一。對於尋找專業光學設備的用戶,這裡的hunting optics真的值得一試。

  • Comment Link can you gamble at foxwoods at 18 Thursday, 09 October 2025 09:28 posted by can you gamble at foxwoods at 18

    canadian approved online casinos, bet365 play blackjack online uk
    and online australian pokies, or buy slot machines australia

  • Comment Link Concrete Contractor in Houston Texas Thursday, 09 October 2025 09:24 posted by Concrete Contractor in Houston Texas

    Wonderful blog! I found it while browsing on Yahoo News.
    Do you have any tips on how to get listed in Yahoo News?

    I've been trying for a while but I never seem to get there!
    Appreciate it

  • Comment Link scam Telegram Thursday, 09 October 2025 09:20 posted by scam Telegram

    OnlyFans Việt Nam leak gây mất an toàn dữ liệu

  • Comment Link SHUjUKuBA.COm Thursday, 09 October 2025 09:02 posted by SHUjUKuBA.COm

    It's very easy to find out any topic on net as compared to textbooks,
    as I found this paragraph at this website. http://shujukuba.com/wp-content/themes/aliyun/inc/go.php?url=https://seconddialog.com/question/decouvrez-nano-pro-lavenir-de-la-protection-des-surfaces/

  • Comment Link SteveWaP Thursday, 09 October 2025 08:30 posted by SteveWaP

    посетить сайт нова маркетплейс

  • Comment Link сертификат на занятия вокалом Thursday, 09 October 2025 07:38 posted by сертификат на занятия вокалом

    Hey fantastic website! Does running a blog like this require a large amount of
    work? I have virtually no expertise in coding however I was hoping
    to start my own blog in the near future. Anyways, should you have
    any recommendations or tips for new blog owners please share.
    I know this is off subject but I just wanted to ask.
    Cheers!

  • Comment Link каркасный дом Thursday, 09 October 2025 07:35 posted by каркасный дом

    This web site really has all the information and
    facts I wanted concerning this subject and didn't know who
    to ask.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.