×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:28

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት። Featured

Rate this item
(0 votes)

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት።

በዚህ ክፍል በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መርኪና የጻፉትን በአጭር በአጭሩ በመጥቀስ እንጨርሳለን።

ዘርና ጎሣ። ጊዜው 1948 ሆኖ ከኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን ጋር እየሠራሁ በነበርኩበት ወቅት ታንዛንያ የተካሄደውን የሉተራን ዓለም ፌዴሬሽን ጉባዔ ለመካፈል አጋጣሚ አገኘሁ …በረርንና ኬንያ ደረስን … በሚቀጥለው ቀን ጧት በአውቶቡስ ተጓዝን …የአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች ሁለት አፍሪካውያን ነበሩ። በአውቶቡሱ ውስጥ አንድ እንግሊዛዊ ከነሚስቱ ተቀምጦ ነበር። ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ለራት ቆምንና ከእንግሊዛዊውና ከሚስቱ ጋር ወደ ምግብ ቤት አመራን። በልተን ስንወጣ ከአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች አንዱ፦ “እናንተ አፍሪካውያን ናችሁ። እዚህ ነጮች ብቻ እንዲገቡ በተፈቀደበት ቤት ለምን ገብታችሁ ትበላላችሁ” አለን። እኛም፣ “በአገራችን እንደዚህ ዓይነት ነገር የተከለከለ አይደለም” አልን። እኛ በዚህ አገር ፍጹም እንግዶች ነን። የኬንያ አሽከርካሪዎች የአዳም ልጆች አይደሉም? የውጪ ዜጎችስ የማን ዘር ናቸው? እንደዚህ ዓይነት የዘር መድልዎ ለእኛ እንግዳ ነገር ነበር። እንደዚህ ዓይነቱን ልዩነት እግዚአብሔር ያስወግድ ብለን ጸለይን። [ገጽ 45]

አሜሪካ በነበርንበት ጊዜ [1957] ዳግመኛ የጥቁርና የነጭ ልዩነት ተነሣ። ልጆቻቸው በተመሳሳይ ትምህርት ቤት አይማሩም፤ በጸሎት ቤት ውስጥ በአንድነት አይቀመጡም፤ በአንድ አውቶቡስም አብረው አይሳፈሩም። ይህ የእግዚአብሔርን ቃል የሚጻረርና ማንም የማይክደው ሃቅ ነው። በአሜሪካ በቆየሁበት ጊዜ የተመለከትኩት አንድ ደካማ ነጥብና በአዕምሮዬ ለተፈጠረብኝ ጥያቄ መልስ ያጣሁለት ቢኖር የቆዳ ልዩነት ጉዳይ ነበር። “ዓለማውያኖች ደስ የሚላቸውን ያድርጉ፤ ነገር ግን ክርስቲያኖች ለምን በጌታ ቃል ላይ አይቆሙም? “የክርስቶስን ፈለግ ለምን አይከተሉም? ክርስቶስ ራስ ሲሆን፣ እኛ ብልቶቹ ነን። ልዩነት የለም፤ የአሜሪካ ክርስቲያኖች ይህን ማሰብ ይኖርባቸዋል።” [ገጽ 91-92]

እኛ ክርስቶስን ስናምን በጎሣና በዘር ልዩነት ነበረን። የእግዚአብሔር ቃል በመጀመሪያ አዳምና ሔዋንን ፈጠራቸው፣ ከእነርሱ የሰዎች ዘር ሁሉ እንደ መጣ ቃሉ ይናገራል። ስለዚህ እኛ አማኞች ከሆንን በኋላ በፊት ከማናገኛቸው ሰዎች ጋር አብረን በላን፣ ጠጣን፤ አንድነት አደረግን። ስለዚህ በአሜሪካን አገር ያላችሁ አማኞች አሳባችሁን ለውጣችሁ ጥቁሮችን ብታስተምሩ ጥሩ ነው።” [ገጽ 176]

በአጋንንት ላይ ሥልጣን። ነባር ቤተክርስቲያን እያጠናከርን፣ ለአዳዲስ ቤተክርስቲያናት ቤት ለመሥራት የሚመች ቦታ እንመርጥ ነበር። በየሄድንበት ቦታ ቃሉን እንሰብካለን። ሾሻ ወደሚባለው አካባቢ ስንደርስ፣ በርኩስ መንፈስ የሚሠቃይ ሰው ነበር። ብዙውን ጊዜ ሰይጣን እሳት ውስጥ እንዲሁም ወንዝ እየወሰደውም ይጥለው ነበር። ጎረቤቶቹም በሰንሰለት ማሰሩ ሰልችቷቸው ነበር። በሰይጣን የተያዘው አቶ ሻለሞ የሚባለው ሰው ሲሆን፣ ከእኔ ጋር አቶ አንጁሎ የሚባል ወንጌላዊ ነበርና ሰውየውን አይቶት መጽሐፍ ቅዱስን በራሱ ላይ ጭነን እንጸልይለት፣ ሰይጣኑም ይለቅቀዋል አለኝ። ወደ እርሱ ስንጠጋ፣ ሰውየው እያለቀሰ ወደ ጓዳ ገብቶ ተደበቀ። እኛም ተከትለነው “በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከእርሱ ውጣ” ብለን ጸለይንና፣ ደግመንም፣ “ይህ የእግዚአብሔር ሰው ነው። በክርስቶስ ደምና በቃሉ እናዝሃለን፤ ለቅቀኸው ውጣ” አልን። መጽሐፍ ቅዱሱንም በላዩ ላይ ጭነን እንደገና ጸለይን። የሰይጣን መንፈስም ለቀቀውና ሰውየው ደህና ሆነ። ሦስት ዓመት ሙሉ በሰንሰለት ታስሮ የኖረ ሰው በጌታ ኃይል ፈውስን አገኘ። [ገጽ 57-58]

እምነት፣ ታማኝነትና መስዋእትነት። መባ አሰጣጣቸው ሁልጊዜ የሚያስደንቀኝ ነበር። በወቅቱ ገንዘብ ያልያዙ ሰዎች ቃል ሲገቡ ይመዘገባሉ። ገንዘብ ይዘው የመጡትም ወዲያው ይከፍላሉ። ባለፈው ዓመት ቃል ገብቶ የነበረ ሰው ገንዘቡን ሳይሰጥ ቢሞት ሚስቱ አምጥታ ትከፍላለች። ለምሳሌ፣ የአቶ ሳቃቶ ሚስት በሞተች ጊዜ ቃል ገብታ የነበረችውን ገንዘብ ባለቤቷ ከፍሏል። አማኞች ሥራቸው ገንዘብ ሰጥተው የወንጌላዊውን ወጪ ችለው መላክ ብቻ አይደለም። የለበሱትን ልብስ አውልቀው ለጌታ አገልጋዮች እንዲሰጥላቸው ያበረክቱ ነበር። ሰዓታቸውንም ከእጃቸው እያወለቁ ይሰጡ ነበር። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ጫማቸውን እያወለቁ ይሰጡ ነበር። በሬ፣ ላምና በቅሎ የሚሰጡም ነበሩ። ልጆች ደግሞ ያረቡትን ዶሮ ይሰጡ ነበር። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ብዙዎች ወንጌላዊ ሆነው ለማገልገል ራሳቸውን ይሰጡ ነበር። ይህን የሚያደርጉት ለጌታ ካላቸው ፍቅር የተነሣ እንጂ ማንም አስገድዷቸው አልነበረም …አቶ ኤካሶም “እኔም አንድ ላም አለችኝ። የላሟን ወተት ግማሽ ለጌታ መስጠት እፈልጋለሁ” አለ። በሚቀጥለው ቀንም ለሁለተኛ ጊዜ ቆሞ፣ “እኔ የላሟን ወተት ከጌታ ጋር መካፈል አልፈልግም። ላሟን እንዳለች ለጌታ ሰጥቻለሁ” አለ …በስብሰባው መጨረሻ ቀን አሁንም አቶ ኤካሶ ተነሥቶ፣ “የወላይታ ቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ቦርድ አባል ከምሆን፣ ወንጌላዊ ሆኜ ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። ጌታ ወደ ላከኝ ቦታ ሁሉ እየሄድኩ ማገልገል የተሻለ ነው። ወንጌላዊ ሆኜ በሕይወቴ ሙሉ ጌታን ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። [ገጽ 59-60፣ 82]  

ገንዘብና አገልግሎት። ወደ ዳሞት ፍላሳ ማኅበር ኮርስ ለመጀመር በምንሄድበት ጊዜ ከአቶ አታሎ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው፣ “የት ትሄዳላችሁ?” ብሎ ጠየቀን። እኛም “ኮርስ ልናስተምር ነው የመጣነው” ብለን መለስን። ሰውዬውም፣ “በሶዶ ዓመታዊ ጉባዔ የሰጠነው ገንዘብ ተልኳል። አሁን ወደ እኛ መንደር ብትመጡ፣ ሌላ ገንዘብ ዳግመኛ የሚሰጣችሁ የለም” አለን። እኛም መልሰን “እኛ ገንዘብ ለመጠየቅ አልመጣንም፣ የመጣነው የእግዚአብሔርን ቃል ልናስተምር ነው፤ አንተም መጥተህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ” አልነው …ስብሰባው ለሦስት ቀን ቀጠለ። አንዲት እኔ የማላውቃት ሴት ሁልጊዜም ስብሰባ ላይ የምትገኝ ስትሆን፣ ከፊት ለፊት ተቀምጣለች። እርሷም በወገቧ ያለውን መቀነቷን ፈታችና ገንዘብ አውጥታ ሰጠች። ቀጥላም የአንገት ልብሷን/ነጠላዋን፣ በቀጣዩም ጊዜ ሻሽዋን ሰጠች። በመጨረሻም፣ የፈረስ መጋለቢያ ሱሪዋን ሰጠች። “ገንዘብ የሚሰጥ የለም” ይል የነበረው ሰው በየቀኑ በበቅሎው ላይ እየተቀመጠ ይመጣና ስብሰባውን ይካፈል ነበር። በቅሎውንም ከደጅ ሣር በሚበላበት ቦታ ያስረዋል። በኮርሱ መጨረሻ ቀን ተነሥቶ ቆመና “አስቀድሜ የምትሰበሰቡት ገንዘብ ለመውሰድ ነው። ማንም ግን የሚሰጣቸው የለም ብዬ ነበር። አሁን የእግዚአብሔር መንፈስ በቅሎዬን እንድሰጥ አሳስቦኛል። ከጌታ መንፈስ ጋር መከራከር አልችልምና በቅሎዬን ሰጥቻለሁ” አለና አምጥቶ ሰጠ። እኛም ጌታን አመሰግን።[ገጽ 79-80]

የሴቶች ጉዳይ። ሴቶች ቸል ይባላሉ ወይ? በቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ክትትል ሚስ በርግስተን ከወላይታ ወረዳ አብያተ ክርስቲያናት ልጃገረዶችን መርጠው መጽሐፍ ቅዱስና እጅ ሥራ ብዙውን ጊዜ ሹራብ ሥራ እንዲማሩ ተደረገ። ሴቶች ወገባቸውን የሚያስሩበትንና ለልጆቻቸውም ደግሞ ሹራብ ይሠራሉ። ሥልጠና አግኝተው የሚሄዱ ልጃገረዶች በተራቸው ሄደው በቤተክርስቲያን የሚገኙትን ሴቶች መጽሐፍ ቅዱስንና የሹራብ ሥራን ያስተምራሉ። [ገጽ 68]

ቤተክርስቲያንና መንግሥት። በ1953 ዓ.ም. አንድ ጊዜ በአካባቢያችን የብዙ ሕዝብ መታሠር ነበር። ክርስቲያኖቹም መልሰው፣ “መንግሥት ሃይማኖት የግል አገር የጋራ መሆኑን በሕገ መንግሥቱ ደንግጓል። እንዴት እንደ ከብት እየነዳችሁን በእስር ቤት ታጉሩናላችሁ?” አሉ …[አዲስ አበባ ሄደን] ማመልከቻ ለማቅረብ ወሰንን። የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘን ከስድስት ኪሎ ወደ ታላቁ ቤተመንግሥት አመራን። ሁላችንም አቤት እያልን እንጮህና እናለቅስ ነበር። ንጉሡም ጩኸታችንንና ለቅሶአችንን ሰምተው ወደ እርሳቸው እንዲያቀርቡን ወታደሮቻቸውን አዘዙ። [ገጽ 132]

ቤተክርስቲያንና ልማት። የወንጌል ሥራና የዕድገት/የልማት ሥራ ጎን ለጎን የሚሄዱ ናቸው። በአውራጃችን ውስጥ መሃይምነትን ለማጥፋት 738 ቤተክርስቲያናት ትምህርት ቤቶችን አዘጋጅተው አስተምረዋል። ዶክተሮች፣ አስተዳዳሪዎች፣ አስተማሪዎች፣ የሕግ ባለ ሙያዎች እና ሌሎች በርካታ ምሁራን ከእነዚያ ቤተክርስቲያን መሥርታ ካስተማረቻቸው ትምህርት ቤቶች የፈለቁ ናቸው። ለወላይታ በዘመናዊ ትምህርት መራመድ በሩን የከፈተችው ቤተክርስቲያን ነች። [ገጽ 123]                              ተፈጸመ።

 

�� ���P�y p ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 1737840 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:46

505967 comments

  • Comment Link download teams Monday, 06 October 2025 07:28 posted by download teams

    microsoft teams ᴡorks perfecty for collaboration. Ι սѕe microsoft teams下载 for grouр tasks.
    Thе teams电脑版 installs easily on my cߋmputer. With microsoft
    teams download, communication iis efficient. І like hоw teams download helps connect ѡith colleagues.
    Ꮃhen hosting teams meeting, tһe audio and videeo quality ԝork reliably.
    Іn conclusion, teams app іs highly recommended.

  • Comment Link Silvia Monday, 06 October 2025 07:25 posted by Silvia

    If you would like to grow your familiarity simply keep visiting this
    website and be updated with the most up-to-date news update posted here. https://365.Expresso.blog/question/levangeliste-une-mission-spirituelle-fondamentale-5/

  • Comment Link JosephTen Monday, 06 October 2025 07:22 posted by JosephTen

    Looking for practical tips on commercial siding? This Commercial Siding resource gives you the essentials. Get clear steps, examples, and things to avoid before you start..

  • Comment Link microsoft teams meeting Monday, 06 October 2025 07:09 posted by microsoft teams meeting

    感谢分享,我最近体验了 teeams 平台,效果真的很棒。无论是使用 teams app 还是 microsoft teams,都能轻松完成远程办公。
    microsoft teams下载 和 teams下载 十分方便,可以直接访问 teams官网 或 teams官网下载。
    teams电脑版、teams电脑版下载 也提供完整功能,还支持 teams中文 界面。用户可以在 teams
    pc 上安装,通过 microsoft teams download 或 teams download 获取。
    想要会议沟通?download microsoft teams、download teams 都很实用,尤其适合 microsoft teams meeting 与 teams meeting。

  • Comment Link 비아그라 효능 Monday, 06 October 2025 07:07 posted by 비아그라 효능

    I just like the helpful information you provide for your articles.
    I'll bookmark your weblog and test once more here frequently.
    I'm quite certain I will learn plenty of new stuff
    proper right here! Best of luck for the following!

  • Comment Link 纸飞机 Monday, 06 October 2025 06:54 posted by 纸飞机

    你好,我最近在使用 telegram,功能真的非常强大。无论是 telegram中文版
    还是 telegram中文版下载,都能轻松上手。
    想要桌面体验?可以试试 telegram电脑版 或 telegram網頁版。很多朋友称它为 纸飞机,实际上 telegram网页版 同样很流畅。

    如果需要安装,直接点 telegram下载,或者访问
    telegram官网 即可。它在国内也叫 电报 或 电报中文。
    telegram下载 与 telegram中文 都是很多用户的选择,同时 telegram 中文版、telegram web 更加适合跨平台使用。

  • Comment Link telegram 中文版 Monday, 06 October 2025 06:44 posted by telegram 中文版

    你好,想要一款安全又强大的通讯工具?推荐 telegram。无论是 telegram中文版 还是 telegram中文版下载,都能满足不同用户需求。
    桌面端也有 telegram电脑版,而且 telegram網頁版 使用起来非常方便,很多人喜欢叫它 纸飞机。
    在网页端,可以直接使用 telegram网页版,下载安装也很简单,只需点 telegram下载 或进入 telegram官网。
    在国内,它也被称为 电报 或 电报中文。不论是 telegram中文,还是
    telegram 中文版,都能获得优秀体验,此外还有 telegram
    web 跨平台使用。

  • Comment Link Lantana-Nagasaki.jp Monday, 06 October 2025 06:35 posted by Lantana-Nagasaki.jp

    Great delivery. Great arguments. Keep up the great spirit.

  • Comment Link telegram中文版 Monday, 06 October 2025 06:17 posted by telegram中文版

    谢谢分享,推荐大家试试 telegram,体验非常好。
    有兴趣的朋友可以使用 telegram中文版 或 telegram中文版下载。
    如果喜欢电脑端体验,可以安装 telegram电脑版,或者直接打开 telegram網頁版,很多人也叫它 纸飞机。
    网页聊天时,用 telegram网页版 最方便。下载安装推荐 telegram下载,也可以去 telegram官网 获取。
    它还有 电报、电报中文 等称呼。不论是 telegram中文、telegram 中文版,还是 telegram web,体验都很流畅。

  • Comment Link stewartmusicfoundation.org lừa đảo công an truy quét cấm gấp người chơi Monday, 06 October 2025 06:14 posted by stewartmusicfoundation.org lừa đảo công an truy quét cấm gấp người chơi

    of course like your web-site however you need to test the spelling on quite
    a few of your posts. Many of them are rife with spelling issues and I to find it very bothersome to
    tell the reality nevertheless I'll certainly come
    again again.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.