×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:28

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት። Featured

Rate this item
(0 votes)

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ። ክፍል ሁለት።

በዚህ ክፍል በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መርኪና የጻፉትን በአጭር በአጭሩ በመጥቀስ እንጨርሳለን።

ዘርና ጎሣ። ጊዜው 1948 ሆኖ ከኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን ጋር እየሠራሁ በነበርኩበት ወቅት ታንዛንያ የተካሄደውን የሉተራን ዓለም ፌዴሬሽን ጉባዔ ለመካፈል አጋጣሚ አገኘሁ …በረርንና ኬንያ ደረስን … በሚቀጥለው ቀን ጧት በአውቶቡስ ተጓዝን …የአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች ሁለት አፍሪካውያን ነበሩ። በአውቶቡሱ ውስጥ አንድ እንግሊዛዊ ከነሚስቱ ተቀምጦ ነበር። ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ለራት ቆምንና ከእንግሊዛዊውና ከሚስቱ ጋር ወደ ምግብ ቤት አመራን። በልተን ስንወጣ ከአውቶቡሱ አሽከርካሪዎች አንዱ፦ “እናንተ አፍሪካውያን ናችሁ። እዚህ ነጮች ብቻ እንዲገቡ በተፈቀደበት ቤት ለምን ገብታችሁ ትበላላችሁ” አለን። እኛም፣ “በአገራችን እንደዚህ ዓይነት ነገር የተከለከለ አይደለም” አልን። እኛ በዚህ አገር ፍጹም እንግዶች ነን። የኬንያ አሽከርካሪዎች የአዳም ልጆች አይደሉም? የውጪ ዜጎችስ የማን ዘር ናቸው? እንደዚህ ዓይነት የዘር መድልዎ ለእኛ እንግዳ ነገር ነበር። እንደዚህ ዓይነቱን ልዩነት እግዚአብሔር ያስወግድ ብለን ጸለይን። [ገጽ 45]

አሜሪካ በነበርንበት ጊዜ [1957] ዳግመኛ የጥቁርና የነጭ ልዩነት ተነሣ። ልጆቻቸው በተመሳሳይ ትምህርት ቤት አይማሩም፤ በጸሎት ቤት ውስጥ በአንድነት አይቀመጡም፤ በአንድ አውቶቡስም አብረው አይሳፈሩም። ይህ የእግዚአብሔርን ቃል የሚጻረርና ማንም የማይክደው ሃቅ ነው። በአሜሪካ በቆየሁበት ጊዜ የተመለከትኩት አንድ ደካማ ነጥብና በአዕምሮዬ ለተፈጠረብኝ ጥያቄ መልስ ያጣሁለት ቢኖር የቆዳ ልዩነት ጉዳይ ነበር። “ዓለማውያኖች ደስ የሚላቸውን ያድርጉ፤ ነገር ግን ክርስቲያኖች ለምን በጌታ ቃል ላይ አይቆሙም? “የክርስቶስን ፈለግ ለምን አይከተሉም? ክርስቶስ ራስ ሲሆን፣ እኛ ብልቶቹ ነን። ልዩነት የለም፤ የአሜሪካ ክርስቲያኖች ይህን ማሰብ ይኖርባቸዋል።” [ገጽ 91-92]

እኛ ክርስቶስን ስናምን በጎሣና በዘር ልዩነት ነበረን። የእግዚአብሔር ቃል በመጀመሪያ አዳምና ሔዋንን ፈጠራቸው፣ ከእነርሱ የሰዎች ዘር ሁሉ እንደ መጣ ቃሉ ይናገራል። ስለዚህ እኛ አማኞች ከሆንን በኋላ በፊት ከማናገኛቸው ሰዎች ጋር አብረን በላን፣ ጠጣን፤ አንድነት አደረግን። ስለዚህ በአሜሪካን አገር ያላችሁ አማኞች አሳባችሁን ለውጣችሁ ጥቁሮችን ብታስተምሩ ጥሩ ነው።” [ገጽ 176]

በአጋንንት ላይ ሥልጣን። ነባር ቤተክርስቲያን እያጠናከርን፣ ለአዳዲስ ቤተክርስቲያናት ቤት ለመሥራት የሚመች ቦታ እንመርጥ ነበር። በየሄድንበት ቦታ ቃሉን እንሰብካለን። ሾሻ ወደሚባለው አካባቢ ስንደርስ፣ በርኩስ መንፈስ የሚሠቃይ ሰው ነበር። ብዙውን ጊዜ ሰይጣን እሳት ውስጥ እንዲሁም ወንዝ እየወሰደውም ይጥለው ነበር። ጎረቤቶቹም በሰንሰለት ማሰሩ ሰልችቷቸው ነበር። በሰይጣን የተያዘው አቶ ሻለሞ የሚባለው ሰው ሲሆን፣ ከእኔ ጋር አቶ አንጁሎ የሚባል ወንጌላዊ ነበርና ሰውየውን አይቶት መጽሐፍ ቅዱስን በራሱ ላይ ጭነን እንጸልይለት፣ ሰይጣኑም ይለቅቀዋል አለኝ። ወደ እርሱ ስንጠጋ፣ ሰውየው እያለቀሰ ወደ ጓዳ ገብቶ ተደበቀ። እኛም ተከትለነው “በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከእርሱ ውጣ” ብለን ጸለይንና፣ ደግመንም፣ “ይህ የእግዚአብሔር ሰው ነው። በክርስቶስ ደምና በቃሉ እናዝሃለን፤ ለቅቀኸው ውጣ” አልን። መጽሐፍ ቅዱሱንም በላዩ ላይ ጭነን እንደገና ጸለይን። የሰይጣን መንፈስም ለቀቀውና ሰውየው ደህና ሆነ። ሦስት ዓመት ሙሉ በሰንሰለት ታስሮ የኖረ ሰው በጌታ ኃይል ፈውስን አገኘ። [ገጽ 57-58]

እምነት፣ ታማኝነትና መስዋእትነት። መባ አሰጣጣቸው ሁልጊዜ የሚያስደንቀኝ ነበር። በወቅቱ ገንዘብ ያልያዙ ሰዎች ቃል ሲገቡ ይመዘገባሉ። ገንዘብ ይዘው የመጡትም ወዲያው ይከፍላሉ። ባለፈው ዓመት ቃል ገብቶ የነበረ ሰው ገንዘቡን ሳይሰጥ ቢሞት ሚስቱ አምጥታ ትከፍላለች። ለምሳሌ፣ የአቶ ሳቃቶ ሚስት በሞተች ጊዜ ቃል ገብታ የነበረችውን ገንዘብ ባለቤቷ ከፍሏል። አማኞች ሥራቸው ገንዘብ ሰጥተው የወንጌላዊውን ወጪ ችለው መላክ ብቻ አይደለም። የለበሱትን ልብስ አውልቀው ለጌታ አገልጋዮች እንዲሰጥላቸው ያበረክቱ ነበር። ሰዓታቸውንም ከእጃቸው እያወለቁ ይሰጡ ነበር። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ጫማቸውን እያወለቁ ይሰጡ ነበር። በሬ፣ ላምና በቅሎ የሚሰጡም ነበሩ። ልጆች ደግሞ ያረቡትን ዶሮ ይሰጡ ነበር። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ብዙዎች ወንጌላዊ ሆነው ለማገልገል ራሳቸውን ይሰጡ ነበር። ይህን የሚያደርጉት ለጌታ ካላቸው ፍቅር የተነሣ እንጂ ማንም አስገድዷቸው አልነበረም …አቶ ኤካሶም “እኔም አንድ ላም አለችኝ። የላሟን ወተት ግማሽ ለጌታ መስጠት እፈልጋለሁ” አለ። በሚቀጥለው ቀንም ለሁለተኛ ጊዜ ቆሞ፣ “እኔ የላሟን ወተት ከጌታ ጋር መካፈል አልፈልግም። ላሟን እንዳለች ለጌታ ሰጥቻለሁ” አለ …በስብሰባው መጨረሻ ቀን አሁንም አቶ ኤካሶ ተነሥቶ፣ “የወላይታ ቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ቦርድ አባል ከምሆን፣ ወንጌላዊ ሆኜ ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። ጌታ ወደ ላከኝ ቦታ ሁሉ እየሄድኩ ማገልገል የተሻለ ነው። ወንጌላዊ ሆኜ በሕይወቴ ሙሉ ጌታን ለማገልገል ራሴን ሰጥቻለሁ። [ገጽ 59-60፣ 82]  

ገንዘብና አገልግሎት። ወደ ዳሞት ፍላሳ ማኅበር ኮርስ ለመጀመር በምንሄድበት ጊዜ ከአቶ አታሎ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው፣ “የት ትሄዳላችሁ?” ብሎ ጠየቀን። እኛም “ኮርስ ልናስተምር ነው የመጣነው” ብለን መለስን። ሰውዬውም፣ “በሶዶ ዓመታዊ ጉባዔ የሰጠነው ገንዘብ ተልኳል። አሁን ወደ እኛ መንደር ብትመጡ፣ ሌላ ገንዘብ ዳግመኛ የሚሰጣችሁ የለም” አለን። እኛም መልሰን “እኛ ገንዘብ ለመጠየቅ አልመጣንም፣ የመጣነው የእግዚአብሔርን ቃል ልናስተምር ነው፤ አንተም መጥተህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ” አልነው …ስብሰባው ለሦስት ቀን ቀጠለ። አንዲት እኔ የማላውቃት ሴት ሁልጊዜም ስብሰባ ላይ የምትገኝ ስትሆን፣ ከፊት ለፊት ተቀምጣለች። እርሷም በወገቧ ያለውን መቀነቷን ፈታችና ገንዘብ አውጥታ ሰጠች። ቀጥላም የአንገት ልብሷን/ነጠላዋን፣ በቀጣዩም ጊዜ ሻሽዋን ሰጠች። በመጨረሻም፣ የፈረስ መጋለቢያ ሱሪዋን ሰጠች። “ገንዘብ የሚሰጥ የለም” ይል የነበረው ሰው በየቀኑ በበቅሎው ላይ እየተቀመጠ ይመጣና ስብሰባውን ይካፈል ነበር። በቅሎውንም ከደጅ ሣር በሚበላበት ቦታ ያስረዋል። በኮርሱ መጨረሻ ቀን ተነሥቶ ቆመና “አስቀድሜ የምትሰበሰቡት ገንዘብ ለመውሰድ ነው። ማንም ግን የሚሰጣቸው የለም ብዬ ነበር። አሁን የእግዚአብሔር መንፈስ በቅሎዬን እንድሰጥ አሳስቦኛል። ከጌታ መንፈስ ጋር መከራከር አልችልምና በቅሎዬን ሰጥቻለሁ” አለና አምጥቶ ሰጠ። እኛም ጌታን አመሰግን።[ገጽ 79-80]

የሴቶች ጉዳይ። ሴቶች ቸል ይባላሉ ወይ? በቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ክትትል ሚስ በርግስተን ከወላይታ ወረዳ አብያተ ክርስቲያናት ልጃገረዶችን መርጠው መጽሐፍ ቅዱስና እጅ ሥራ ብዙውን ጊዜ ሹራብ ሥራ እንዲማሩ ተደረገ። ሴቶች ወገባቸውን የሚያስሩበትንና ለልጆቻቸውም ደግሞ ሹራብ ይሠራሉ። ሥልጠና አግኝተው የሚሄዱ ልጃገረዶች በተራቸው ሄደው በቤተክርስቲያን የሚገኙትን ሴቶች መጽሐፍ ቅዱስንና የሹራብ ሥራን ያስተምራሉ። [ገጽ 68]

ቤተክርስቲያንና መንግሥት። በ1953 ዓ.ም. አንድ ጊዜ በአካባቢያችን የብዙ ሕዝብ መታሠር ነበር። ክርስቲያኖቹም መልሰው፣ “መንግሥት ሃይማኖት የግል አገር የጋራ መሆኑን በሕገ መንግሥቱ ደንግጓል። እንዴት እንደ ከብት እየነዳችሁን በእስር ቤት ታጉሩናላችሁ?” አሉ …[አዲስ አበባ ሄደን] ማመልከቻ ለማቅረብ ወሰንን። የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘን ከስድስት ኪሎ ወደ ታላቁ ቤተመንግሥት አመራን። ሁላችንም አቤት እያልን እንጮህና እናለቅስ ነበር። ንጉሡም ጩኸታችንንና ለቅሶአችንን ሰምተው ወደ እርሳቸው እንዲያቀርቡን ወታደሮቻቸውን አዘዙ። [ገጽ 132]

ቤተክርስቲያንና ልማት። የወንጌል ሥራና የዕድገት/የልማት ሥራ ጎን ለጎን የሚሄዱ ናቸው። በአውራጃችን ውስጥ መሃይምነትን ለማጥፋት 738 ቤተክርስቲያናት ትምህርት ቤቶችን አዘጋጅተው አስተምረዋል። ዶክተሮች፣ አስተዳዳሪዎች፣ አስተማሪዎች፣ የሕግ ባለ ሙያዎች እና ሌሎች በርካታ ምሁራን ከእነዚያ ቤተክርስቲያን መሥርታ ካስተማረቻቸው ትምህርት ቤቶች የፈለቁ ናቸው። ለወላይታ በዘመናዊ ትምህርት መራመድ በሩን የከፈተችው ቤተክርስቲያን ነች። [ገጽ 123]                              ተፈጸመ።

 

�� ���P�y p ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 1702668 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:46

498415 comments

  • Comment Link Robertwaymn Friday, 26 September 2025 22:01 posted by Robertwaymn

    Dr. Jake Scott is on the front line of his second pandemic in five years and he is not getting much sleep.

    Scott works full-time as an infectious disease physician at Stanford Health Care’s Tri-Valley hospital in Pleasanton, California. When he is done taking care of his patients and his two grade-school aged kids, he often stays up past midnight writing — furiously penning op-eds, collecting studies, leading evidence reviews and posting meaty threads on social media, most of them correcting the record on vaccines.
    трипскан вход
    Often, he’s reacting to the latest maneuvers by US Health and Human Services Secretary Robert F. Kennedy Jr.. A pinned post responding to one of Kennedy’s appearances on Fox News has been viewed almost 5 million times. Another post fact-checking Kennedy’s claims about potential harms from aluminum in vaccines had 1 million views in its first 48 hours. Scott’s followers on X have doubled since April.
    https://tripscan43.biz
    tripskan
    “A million views for this long-winded, very detailed, kind of nerdy breakdown of the science,” Scott said, marveling at the attention it got. “I think that’s saying something, you know? People want that information, and they deserve it,” said Scott who is 48.

    The Covid-19 pandemic turned many infectious disease specialists and virologists into household names. Scott’s was not one of them, perhaps because he was too busy treating patients. He didn’t stay out of the public discourse completely, however. He was one of the first doctors to tell people that Omicron didn’t seem to be as severe an infection as earlier strains of the virus, although some virologists were skeptical at the time.

    In President Donald Trump’s second administration, however, Scott is taking on what he sees as a second pandemic — misinformation and disinformation about vaccines. He knows false information can be as harmful as any virus.
    “When officials spread inaccurate information about vaccines, it does have real consequences, and families make decisions based on fear rather than on facts,” Scott said.

    It’s already happening. The US Centers for Disease Control and Prevention recently reported data showing kindergarten vaccination rates continue to decline, as states make it easier to opt out of school vaccination requirements. Vaccine preventable diseases like measles and whooping cough are rising again, too.

    Scott knows it could get much worse.

    “In 2021, nearly every single patient I lost to Covid was unvaccinated by choice, and every colleague of mine has said the same thing.”

  • Comment Link ibuprofenblog Friday, 26 September 2025 21:50 posted by ibuprofenblog

    Be sensitive about ED patients. [url=https://www.ibuprofenbloginfo.com/ ]ibuprofenbloginfo.com[/url] . More info’s awaits you. sertraline interactions

  • Comment Link ibuprofenblog Friday, 26 September 2025 21:46 posted by ibuprofenblog

    Stay home, shop your drugs online and enjoy a low price of [url=https://ibuprofenbloginfo.com/ ]http://www.ibuprofenbloginfo.com[/url] Read treatments of ED! sertraline tablets

  • Comment Link login bola slot Friday, 26 September 2025 21:45 posted by login bola slot

    This is a topic which is close to my heart...

    Thank you! Exactly where are your contact details though?

  • Comment Link youdao download Friday, 26 September 2025 21:02 posted by youdao download

    I recently explored 有道 ɑnd found it to be ɑ very helpful translation platform.
    Тһe site offers official 有道下载 ɑnd 有道翻译下载
    options, making it fаѕt to start translating. Many սsers love 有道翻译 ɑnd youdao bеcause
    it supports multiple languagess ѡith accuracy. Additional tools ⅼike 有道词典, 有道云, and 网易有道翻译 enhancce productivity.
    Foor desktop սsers, 有道翻译电脑版 andd youdao download prrovide smooth performance.
    Ԝhether it’s 翻译有道 оr 有道翻译官网, this site iѕ
    trusted for anyone ⅼooking foг official translation solutions.

  • Comment Link slot jackpot Friday, 26 September 2025 20:49 posted by slot jackpot

    When someone writes an paragraph he/she keeps the plan of a user in his/her
    brain that how a user can understand it. So that's why this article is great.
    Thanks!

  • Comment Link Car Key Jammed Repair Friday, 26 September 2025 20:43 posted by Car Key Jammed Repair

    What's The Job Market For Car Key Jammed Repair Professionals?

    Car Key Jammed Repair

  • Comment Link VU88 Friday, 26 September 2025 20:38 posted by VU88

    Nạp tiền xong vào tài khoản ngay, không cần chờ đợi lâu như mấy chỗ khác.

  • Comment Link 爱思助手下载 Friday, 26 September 2025 19:30 posted by 爱思助手下载

    Had the chance to explore 爱思助手 ɑnd found it very uѕeful for iPhhone and iPad ᥙsers.
    The platform mаkes itt easy to access the official 爱思助手下载,
    ensuring secure device management. Manyy people prefer 爱思 ƅecause iit
    helps with backups, updates, ɑnd app installations іn а
    simple wаy. Anpther helpful option here is i4助手, whicһ pгovides reliable
    solutions fοr Applle devices. Ϝoг all kinds of users, І4 іs
    powerful, mаking it a reliable management tool. Ꭰefinitely suggеѕt this site iff ʏou want an safe source for downloads аnd iOSsupport.

    Overall, iosais.com iѕ a great resource fߋr Apple fans.

  • Comment Link Журнал Коллекция идей | Журнал Коллекция идей Friday, 26 September 2025 19:22 posted by Журнал Коллекция идей | Журнал Коллекция идей

    Статья предоставляет информацию из разных источников, обеспечивая балансированное представление фактов и аргументов.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.