dead branches

ወ  ፍ   እ  ና   ማ  ለ  ዳ

እንኳንስ ችግኙ፥ ሰዎች የተከሉት

ሥር ይይዝ ነበረ፥ አዕዋፍ የዘሩት።

ዘንድሮ ግን ወፎች፥ እንኳንስ ሊዘሩ

ናፍቆኛል ማለዳ፥ መስማት ሲዘምሩ።

ወፎች ከማለዳ -

በምን ተቃቃሩ?!

ፅልመቱ ሲገፈፍ -

እንዳላበሰሩ፤

ማዜም ተስኗቸዉ -

ተዘግቶ ጀንበሩ

ወደሚነጋበት -

ወዴትስ በረሩ?!

~ አብደላ ዕዝራ

pic credit: pinterest.com